Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

Author: Yonas Habesha

ባለስልጣኑ ከሲዳማ ክልል ለተውጣጡ አመራሮች የሪፎርም ትግበራ ልምዱን አካፈለ።

(ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን ከሲዳማ ክልል ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች የተቋሙን የአስተዳደርና አገልግሎት ማሻሻያ ሪፎርም አተገባበር ልምድ እና ያገኛቸውን በጎ ውጤቶች አካፈለ።

በመድረኩ ላይ የሪፎርም አፈጻጸም ሰነዱን ያቀረቡት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለጹት ተቋሙ የሪፎርሙን የትግበራ ጊዜን በውጤታማነት እየተወጣ የሚገኝ የገለጹ ሲሆን አሁን ላይ የተገኘውን ስኬት ወደ ማጽናት ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ ተግባራትን እያከናወነ አብራርተዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም ባለስልጣኑ በተለይም የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት፣ ተቋማዊ አደረጃጀትን በማስተካከል፣ የሰው ሀይልን በብቃት ማበልጸግ እና አሰራሮችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ ረገድ ጠንካራ እና ለዋጭ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል።

ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ የሪፎርም ትግበራው ዋና ዋና አፈጻጸሞች እና የተገኙ ውጤቶችን በተለይም የህግ ማዕቀፎች እና የአሰራር ስርዓት ማሻሻያን በገለጹበት ገለጻ አዲሱን የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1333/2016 መነሻ በማድረግ የግዥ አፈጻጸም፣ የመድኃኒትና ህክምና መሳሪያዎች፣ የመንግስት ልማት ድርጅቶች እና የንብረትና ተሸከርካሪ አስተዳደር መመሪያዎች ተዘጋጅተው በስራ መዋላቸውን እና የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ የጨረታ መደበኛ ሰነዶች (SBD)፣ የአቤቱታና ይግባኝ አቀራረብ ማንዋሎች እንዲሁም ዘላቂነት ያለው የግዥ ስርዓት (Sustainable Procurement) ማንዋል ተዘጋጅተው ስራ ላይ እንደዋሉ አመላክተዋል።

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የኤሌክትሮኒክ የመንግስት ግዥ (e-GP) ስር ዓት ትግበራ፣ የተሸከርካሪ ቁጥጥር እና ንብረት ቁጥጥር (e-Fleet) እና ሌሎች ዲጂታል ስራዎችን በከፍተኛ ዲስፕሊን እየተገበረ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

ባለስልጣኑ የሪፎርም ውጤታማነቱን ለማስቀጠል የሰው ሀይል ብቃትን ማሳደግ እንዲሁም ብዝኃነት እና አካታችነት መተግበር አስፈላጊ በመሆኑ ሰራተኞችን የማብቃትና አካታችነቱን እንዲጠብቅ የማድረግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ተብራርቷል።

በቀጣይም ባለስልጣኑ እስካሁን ያገኛቸውን የዲጂታላይዜሽን እና የተቋማዊ ሪፎርም ስኬቶች በማጠናከር፣ የዲጂታል አሰራሩን ወደ ሁሉም ክልሎች የማስፋፋት፣ የአገልግሎት ጥራትን የማሳደግ እና ግልጽና ተጠያቂነት ያለው አሰራርን የመገንባት ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተገለጸ ሲሆን የሲዳማ ክልል አመራሮችም ባለስልጣኑ እየተገበረ በሚገኘው የሪፎርም ስራ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሄዱ::

(ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች በክረምት የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር ማዕቀፍ ውስጥ በመሳተፍ በዛሬው እለት  የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሂደዋል።

ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ በክረምት ወቅት ህብረተሰቡን የሚጠቅሙ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን ለማከናወን አቅዶ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ቀደም ሲል የተጀመረው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አንዱ ሲሆን በዛሬው እለት የተካሄደው የደም ልገሳ መርሃ ግብርም የዚህ የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ አካል እና የቀጣይ በጎ አድራጎት ስራዎች ማስቀጠያ መርሃግብር ነው።

በቀጣይ የክረምት ወራትም ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተለያዩ የበጎ አድራጎት መስኮች ላይ ተሳትፎውን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። በተለይም የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስና መገንባት፣ የመማሪያ ቁሳቁስ ማሟላት ለማይችሉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት፣ ለአረጋውያንና ለአቅመ ደካሞችን የምግባ መርሃግብር ማካሄድ እና ሌሎች መሰል ህብረተሰብ አቀፍ የበጎ አድራጎት ተግባራትን ለማከናወን ዝግጅቶች ተጠናቀው እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ።   

የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች በክረምት የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ የሚያሳዩት ንቁ ተሳትፎና ተነሳሽነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚቀጥል ይሆናል።

በኮንትራትማኔጅመንትዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠናተጠናቀቀ።

(ሀምሌ 11/2018 ዓ.ም)፣ በኮንትራት ማኔጅመንት (ውል አስተዳደር) ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የስልጠና መድረክ በስኬት ተጠናቋል። በድረኩ ማጠቃለያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቅሌ ባደረጉት ንግግር ስልጠናው በዘርፉ ያሉ የአሰራር ክፍተቶችን ለመሙላት እና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አስገንዝበዋል።

ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ በንግግራቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የገጠር መንገድ ፕሮጀክቶች የህዝብን ህይወት የሚቀይሩ መሰረታዊ የልማት ፕሮግራሞች መሆናቸው፣ የኮንትራት ማኔጅመንት አሰራርን ማዘመን እና ከጨረታ ሰነድ ዝግጅት መጀመር አስፈላጊ መሆኑ፣ የዋጋ ማሻሻያ (Variation Order) እና የጊዜ ማራዘሚያ (Time Extension) ቁጥጥር አስፈላጊ መሆኑ፣ የፕሮጀክት ጥራት ቁጥጥር እና የተቋማት ቅንጅት ለማንኛውም ስራ ስኬት መሰረት መሆኑ፣ የግዥ ህግ ልማትን እንደማያደናቅፍ ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑ ተብራርቷል።

ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ በማጠቃለያቸውም ከዚህ ስልጠና የተገኙ እውቀቶችና የጋራ ተሞክሮዎች ወደ ስራ ሲመለሱ በሚገባ ሪቪው (Review) ሊደረጉ እንደሚገባ አሳስበዋል። የስልጠናውና የሁለት ቀኑ ውይይት ትክክለኛ ውጤት ሊለካ የሚችለው በስራዎች ጥራት፣ የፕሮጀክት መዘግየት ጊዜ ሲቀንስ፣ የተሻሻለ የኮንትራት አስተዳደር ሲኖር እና በተቋማት ቅንጅት አማካኝነት የህዝባችንን እርካታ ማረጋገጥ ሲቻል ብቻ በመሆኑ ሁሉም አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ባለስልጣኑየኮንትራትማኔጅመንትአቅምንለማጠናከርያለመስልጠና እየሰጠ ነው።

(ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም)፣ የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በገጠር ትሥር ኮኔክቲቪቲ (Rural Connectivity) ፕሮግራም ማዕቀፍ ውስጥ የሚፈጸሙ የኮንትራት ፕሮጀክቶችን በተሻለ ብቃት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ለመምራት የሚያስችል ሀገራዊ የኮንትራት ማኔጅመንት ስልጠና መድረክ ከፍቷል።

የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለጹት ይህ መድረክ በክልል መንገድ ዘርፍ፣ በፋይናንስ ተቋማት እና በክልል ግዥ ባለስልጣናት መካከል የጋራ ግንዛቤን ለማጠናከርና በፕሮጀክት አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።

ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ በንግግራቸው የገጠር ትስስር (Rural Connectivity) ፕሮግራም የገጠር ማህበረሰቡን ከኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አገልግሎቶች ጋር በማገናኘት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ወሳኝ ሀገራዊ ፕሮግራም መሆኑን ጠቅሰዋል። የገጠር መንገዶችና የመጓጓዣ መሠረተ ልማቶች የገበያ ተደራሽነትን፣ የግብርና ምርትን፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎትን እንዲሁም የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያፋጥኑ መሠረታዊ የልማት መሣሪያዎች መሆናቸውንም አብራርተዋል።

“እያንዳንዱ የሚገነባ ኪሎ ሜትር መንገድ በዜጎቻችን የኑሮ ጥራት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ አለው” ያሉት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የፕሮጀክቶች ስኬት ግን በጀት በመመደብ ብቻ እንደማይረጋገጥ ይልቁንም ጥራት ያለው የግዥ ሂደት፣ ውጤታማ የኮንትራት አስተዳደር፣ ወቅታዊ ክትትል፣ ትክክለኛ የፋይናንስ አያያዝ እና ጠንካራ የተቋማት ቅንጅት በአንድነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ዛሬ በአለም አቀፍ ደረጃ የመንግስት ግዥ ዓላማ ከዝቅተኛ ዋጋ አሰራር ወጥቶ ወደ “Value for Money” (ለገንዘብ ተገቢውን ዋጋ ማግኘት)፣ ዘላቂነት፣ እና የህይወት ዑደት ወጪ ትንተና (Life Cycle Cost Analysis) ላይ ትኩረት እያደረገ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። ባለስልጣኑም ይህንን መሠረት በማድረግ የግዥ ሥርዓቱ ቀልጣፋ፣ ግልጽ፣ ተወዳዳሪና ተጠያቂነት ያለው እንዲሆን የህግ ማዕቀፎችንና የቴክኖሎጂ አሰራሮችን በመዘርጋት የተቋማትን አቅም ለመገንባት በስፋት እየሰራ ይገኛል።

በውይይቱ በኮንትራት ማኔጅመንት ውስጥ የለውጥ ትዕዛዞችን (Variation Orders) በአግባቡ ማስተዳደር፣ የጊዜ ማራዘሚያ ጉዳዮችን በአግባቡ መመርመር እና ክፍያዎችን በግልጽነት መፈጸም የፕሮጀክቶችን ስኬት እንደሚወስኑ የተገለጸ ሲሆን ሊያጋጥሙ የሚችሉ የዋጋ መለዋወጥ፣ የአየር ጸባይና የቴክኒክ ስጋቶችን (Risks) ቀድሞ በመለየት የጥንቃቄ ስልቶችን ማስቀመጥ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል።