Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

Author: Yonas Habesha

የስነ- ምግባርና ፀረ- ሙስና ቀን በደማቅ ስነስርዓት ተከበረ። 

(ሕዳር 29/2018 ዓ.ም)፣ የገንዘብ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋምት በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛው የሚከበረውን በስሩ የስነ- ምግባርና ፀረ- ሙስና ቀን “ትውልድን በስነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር’’ በሚል መሪ ቃል አክብረዋል፡፡

በክብረ በዓሉ የመክፈቻ ንግግር ያደረኩት የገንዘብ ሚንስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ ፍቃዱ ሆሮታ ሲሆኑ በዓሉን ከማክበር በዘለለ ሁሉም ሰው በተሰጠው ሀላፊነት ትርጉም  ያለው ስራ መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። ክቡር አቶ ፈቃዱ በዚህ መንግስት ሙስናን ለመከላከል የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝና ትውልድን በስነ-ምግባር በማነፅ በኩልም ከፍተኛ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

በሌላ በኩል ከስነ- ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን ተወከልው የተገኙት አቶ የኋላሸት በበኩላቸው ሙስና ሀገርንም ትውልድንም የሚያቀጭጭና አሳሪ ተግባር በመሆኑ ሁሉም ሊዋጋው ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

መልዕክታቸውን ተከትሎ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሚኒስቴሩ እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች የሀብት ምዝገባ ማሳወቂያ ሰነድ ለኮሚሽኑ ተወካዮች የማስረከብ ሥነ- ሥርዓት ተካሂዷል።

በዕለቱ የስነ- ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን ያዘጋጀው ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በጥናታዊ ጽሁፉ ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበውም ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

Gender-responsive public procurement has been promoted in the proclamation and procurement Directive that Women will benefit from special condition. H. E. Mrs. Meseret Meskele

A discussion forum on gender-responsive public procurement was held on November 27, 2025, at the Adama Executive Hotel. The discussion centered on an assessment report presented by Hiwot Bahru, a consultant at the UN Women Ethiopia office, focusing on the status and gaps of gender-responsive procurement in the country.

The discussion was officially opened by H. E.  Mrs. Meseret Meskele, Director General of the Federal Public Procurement and Property Authority, who emphasized the government’s commitment in promoting inclusive and equitable procurement practices.

Participants were selected from key institutions including the Federal Public Procurement and Property Authority, Federal Public Procurement Service, the Ministry of Finance, the Ministry of Women and Social Affairs, cooperatives, professional associations, and other stakeholders.

Findings from the assessment highlighted the need for stronger measures to enhance women’s participation in public procurement. The report also stressed the importance of improving access to public information and creating an enabling environment for women-led enterprises.

ባለስልጣኑ ቀልጣፋ አገለግሎት መስጠት የሚያስችል ስርዓት እየገነባ መሆኑ ተገልጸ።

(ህዳር 17/2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስርዓት እየገነባ መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ገልጸዋል። ዋና ዳይሬክተሯ ይህን የገለጹት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን የመስክ ምልከታ ባደረጉበት ወቅት ነው።

የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የባለስልጣኑን የስራ እንቅስቃሴ የተመለከተ ሲሆን ባለፉት አራር ወራት የተሰሩ አበይት ክንውኖችንም አዳምጧል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት በሪፖርታቸው ተቋሙ የአሰራር ስርዓቱን በማዘመን ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ የዲጂታል ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን የገለጹ ሲሆን የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ፣ ዲጂታል የአስተያየት መስጫ፣ ዲጂታል የቅሬታ ማስተናገጃ፣ ዲጂታል የብልሹ አሰራርና የሙስና ጥቆማ መስጫ፣ ዲጂታል የኦዲት አገልግሎትና የነዳጅና ተሽከርካሪ ስምሪት በምሳሌንት ተነስተዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሪፎርም የትግበራ ምዕራፍ ላይ መሆኑን አንስተው በዚህም የተቋማዊ ለውጥ ማኑዋል፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ፣ የስርዓተ ጾታና ማህበራዊ ማካተቻ ማኑዋል እና ሌሎች ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የመንግስት ግዥን እና ንብረት አስተዳደርን ዘመናዊ በማድረግ የሀገር ሀብት ከብክነት ለመታደግና ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ከፍተኛ ዋጋ እንዲያስገኝ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። በዚህ ረገድ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ትልቅ ሚና እየተጫወት እንዳለና ስርዓቱም ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በሁሉም የፌዴራል ተቋማት ተግባራዊ መደረጉን አመላክተዋል።

ከገለጻው በኋላ ቋሚ ኮሚቴው የመስክ ምልከታውን ያካሄደ ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥራትና ቅልጥፍናን የተቋሙ ባህል ለማድረግ እያከናወነው የሚገኘውን የዲጂታል ስራ የሚበረታታ መሆኑን በግበረ መልሳቸው አሳይተዋል።

ባለስልጣኑ የሪፎርም የትግበራ ምዕራፉን በብቃት እየተገበረ እንደሚገኝ ተገለጸ።

(ህዳር 14/2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የሪፎርም የትግበራ ምዕራፍን በብቃት እየተወጣ ነው ሲሉ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ገልጸዋል። ዋና ዳይሬክተሯ ይህን የተናገሩት የተቋሙን የአገልግሎት ስነ- ምድብ (Service Taxonomy) በሚመለከት ከባለስልጣኑ ሰራተኞች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት በተደረገበት ወቅት ነው።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት በንግግራቸው በትግበራ ምዕራፉ ይሰራሉ ተብለው ከተያዙ ጉዳዮች አንዱ የዲጂታል ስራዎች ማስፋት መሆኑን አንስተው በዚህም የአገልግሎትን ጥራትና ቅልጥፍና ሊጨምሩ የሚችሉ የዲጂታል ስራዎች መልማታቸውን አብራርተዋል። ከዚህም በተጨማሪ የአደረጃጀት ስራዎች፣ የአቅም ግንባታ ስራዎች፣  ማኑዋሎች፣ የስልጣን ሞጁሎች፣ የአገልግሎት አስጣጥ ጥራትንና ቅልጥፍናን ሊያሳድጉ የሚችሉ የአሰራር ስርዓቶች፣ መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል።

በተቋሙ የአገልግሎት ስነ- ምድብ (Service Taxonomy) ላይ ገለጻ ያደረጉት የባለስልጣኑ ስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳን ኤል ገረመው በበኩላቸው ባለስልጣኑ የሚሰጠው አገልግሎት ስነ ምድብ የተዘጋጀለት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድም እንደወጣላቸው አመላክተዋል። አቶ ዳንኤል በገለጻቸው ባለሙያው የሚለካው በሚሰጠው አገልግሎት ብቻ ሳይሆን አገልግሎት አሰጣጡ ስታንዳርዱን መሰረት በማድረግ የተሰጠ መሆኑና ስታንዳርዱ በሚያስቀምጠው ጊዜ፣ መጠን እና ጥራት ልክ መሆኑን በማረጋገጥ ጭምር መሆኑን አመላክተዋል።

በመጨረሻም ከሰራተኛው የተለያዩ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን በክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እና በአቶ ዳን ኤልገረመው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል።