Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

News

የ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመትን በማስመልከት ከኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የተላለፈ መልዕክት

ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የተቋማችን ተገልጋዮች፣ ባለድርሻ አካላት፣ አቅራቢዎች፣ የልማት አጋሮችና የግዥ ማኅበረሰብ፣

እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና፣ በደስታና በተስፋ አደረሳችሁ!

አዲስ ዓመት ያለፈውን በመገምገም፣ ከተሞክሮአችን በመማርና ለተሻለ ነገ አዲስ ተስፋና ቁርጠኝነት የምንሰንቅበት ወቅት ነው። 2019 ዓ.ም. ለሀገራችን የሰላም፣ የአንድነት፣ የእድገትና የብልጽግና ዓመት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ።

የፌዴራል የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን በአዲሱ ዓመትም የመንግሥት ግዥና  ንብረት አስተዳደር ሥርዓትን የበለጠ ግልጽ፣ ተጠያቂ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊና ዘመናዊ ለማድረግ በቁርጠኝነት ይሰራል።

በተለይም የኢ-ግዥ ሥርዓታችንን በማጠናከር፣ የዲጂታል ለውጡን በማፋጠን፣ የተገልጋዮችን የአገልግሎት ልምድ በማሻሻል፣ የግዥ ሥርዓቱን በተገቢው መልኩ በማስተዳደርና የሕዝብ ሀብት በብቃትና በተጠያቂነት እንዲጠቀም በማድረግ የበለጠ ውጤት ለማምጣት ተዘጋጅተናል።

ይህንን የለውጥ ጉዞ ለማሳካት የመንግሥት ተቋማት፣ አቅራቢዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ባለሙያዎች፣ ተገልጋዮችና መላው ሕዝብ የሚያደርጉት ትብብርና ተሳትፎ ወሳኝ ነው። ለምታደርጉት ትብብር፣ ድጋፍና ገንቢ ግብረመልስ ከልብ አመሰግናለሁ።

የህዝብ ሀብት የጋራ ሀብታችን ነው፤ የሕዝብ እምነትም የጋራ ኃላፊነታችን ነው። በታማኝነት፣ በሙያዊ ብቃት፣ በፈጠራና በትብብር የተሻለ የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት በጋራ እንገንባ።

በድጋሚ፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለተገልጋዮቻችንና ለሁሉም ባለድርሻ አካላት የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የተስፋና የብልጽግና ዓመት እንዲሆን እመኛለሁ።

እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት አደረሳችሁ!

መልካም አዲስ ዓመት!

ባለስልጣኑ የ“ህብር ቀን”ን ከዝቅተኛ ተከፋይ ሰራተኞች ጋር አከበረ።

(ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም| አዲስ አበባ) – የፌደራል የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን “የህብር ቀን”ን እና የ2019 አዲስ አመትን አስመልክቶ ከተቋሙ ዝቅተኛ ተከፋይ ሰራተኞች ጋር ያከበረ ሲሆን ለሰራተኞቹም ልዩ ልዩ ስጦታዎችን አበርክቷል።


ባለስልጣኑ በክረምቱ ወራት የተለያዩ ማህበራዊ ተግባራትን ሲያከናውን የቆየ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በተለይም በሜቄዶኒያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን ማዕከል በመገኘት የምገባ መርሃ ግብር ማካሄዱ እንዲሁም በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሩ ካከናወናቸው ማህበራዊ ሀላፊነቶች በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው።


በመድረኩ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በንግግራቸው መተሳሰብ፣ መተጋገዝ እና መተባበር የቆየና የጠነከረ ኢትዮጵያዊ እሴት መሆኑን አውስተዋል። አክለውም ሰራተኞቹ የደመወዛቸው ዝቅተኛ መሆን ሳይገድባቸው ለተቋሙ ስኬት ላበረከቱት አስተዋጽዖ እና ላሳዩት የላቀ ትጋት የከበረ ምስጋና አቅርበዋል።

“እያንዳንዱ የተቋማችን ተግባር እርስ በእርስ የተሳሰረ በመሆኑ በቅንጅት ስንሰራ ውጤታማነታችን ይጎላል” ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ ተቋሙ ሁልጊዜም ቢሆን ከሰራተኞቹ ጎን እንደሚቆም አረጋግጠዋል።


በመጨረሻም በመጪው 2019 አዲስ ዓመት ሰራተኞቹ የበለጠ በተነሳሽነት፣ በቅንነትና በታማኝነት አገልግሎት የሚሰጡበት የመተሳሰብና የስኬት ዘመን እንዲሆንላቸው የአዲስ ዓመት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

ባለስልጣኑ የ2019 የአዲስ ዓመት ዋዜማን እና የ2018 በጀት ዓመት ስኬቶችን የሚገልጽ ልዩ የአብሮነት መርሃ-ግብር አካሄደ።

(ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም|አዲስ አበባ) – የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የሰራተኞችን ተነሳሽነት ለማሳደግ፣ አብሮነትን ለማጠናከር እና የ2019 የአዲስ ዓመት ዋዜማ ለማከበር ያለመ ልዩ የአብሮነት መርሃ-ግብር አካሄደ።


በመርሃ-ግብሩ ላይ በ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ አበይት ሁነቶችን እንዲሁም የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ሂደት፣ አፈጻጸምና ስኬቶችን የሚያሳዩ አጫጭር ቪዲዮዎች ለታዳሚው ቀርበዋል። ከዚሁ ጎን ለጎንም በሰራተኞች መካከል መቀራረብን የሚያጠናክሩ የጠቅላላ እውቀትና ተቋማዊ ጥያቄና መልስ ውድድር የተካሄደ ሲሆን የ2019 ዓ.ም እቅድና የቃል መግባት መርሃ-ግብርም ተከናወኗል።


በመድረኩ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ለአዲሱ የ2019 ዓ.ም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ዋና ዳይሬክተሯ በንግግራቸው ባለስልጣኑ በ2018 በጀት ዓመት በርካታ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመው ለተመዘገቡት ስኬቶች መላው የባለስልጣኑን ማህበረሰብ አመስግነዋል። ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም “አዲሱ ዓመት አብሮነታችንን እና ትጋታችንን የበለጠ አጠናክረን የባለስልጣኑን ራዕይ እውን የምናደርግበት እንዲሆን እየተመኘሁ፣ በግል ህይወታችሁም ስኬታማ እንድትሆኑ ከልብ እመኛለሁ” ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ ከባለስልጣኑ አመራርና ሰራተኞች በተጨማሪ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ላይ ልምድ ልውውጥ ላይ የሚገኙት የናይጀሪያ የመንግስት ግዥ ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላትም ተገኝተዋል።


የልዑካን ቡድኑ ተወካይ በድረኩ ባደረጉት ንግግር ባለስልጣኑ ላደረገላቸው ሞቅ ያለ አቀባበል እና ላካፈላቸው ልምድ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበው “በተለይም በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት ዋዜማ በዚህ መልኩ ከባለስልጣኑ አመራርና ሰራተኞች ጋር ማክበር በመቻላችን እጅግ ደስተኞች ነን” ሲሉ ገልጸዋል።

Federal Public Procurement and Property Authority shared it best practices on Electronic Government Procurement system.

(7 sep. 2026| Addis Ababa) — The Federal Public Procurement and Property Authority (FPPPA) hosted a delegation from the Public Procurement Authority of Nigeria for a high-level peer-to-peer knowledge exchange focused on Electronic Government Procurement (e-GP) systems.

FPPPA Director General, H. E. Mrs. Meseret Meskele, welcomed the delegates and delivered the opening address, highlighting the current situation and overall strategic direction of Ethiopia’s public procurement and property management systems. Emphasizing that digital transformation goes beyond digitizing procedures, she framed technology as a vital tool to strengthen transparency, efficiency, and accountability.

She also emphasized that one of the important areas of our e-GP development is integration of the procurement system with other government digital platforms and Such integration is essential for creating a connected government ecosystem, reducing duplication, improving data exchange, and making public services more efficient.

H.E. incorporate that sharing knowledge, experiences, innovations, and practical solutions with African brothers’ is more crucial to improve gaps and to become more efficient and competent.

During the session, Mr. Yafet Mekonnen, e-GP Project Manager, delivered a comprehensive presentation detailing the operational rollout and execution overview of Ethiopia’s e-GP system. At the discussion, the Nigerian delegation raised technical and strategic questions regarding implementation strategies, to which FPPPA officials provided clarifications.