Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

General

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።

(ሰኔ 19/2017 ዓ.ም )፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአሰራር ስርዓቱን ለማዘመንና ቅንጅታዊ አሰራርን ለማሳደግ በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማ ፒራሚድ ሆቴል ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል። 

በውይይቱ ላይ ባለስልጣኑ መስሪያ ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት የተተገበሩ አበይት ተግባራት በዋና ዳይሬክተሯ ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን የ2018 እቅድና እና ሌሎች የሪፎርም ስራዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ይሆናል።

በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ከሁሉም የፌደራል ባለበጀት መ/ቤቶች ጋር ውይይት ተካሄደ።

(ሰኔ 17/2017 ዓ.ም)፣ የፌዴራል የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከሁሉም የፌደራል ባለበጀት መ/ቤቶች የሥራ ኃላፊዎች እና የግዥና ንብረት ኃላፊዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ዙሪያ በጋራ ለመገምገም እና የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድን የጋራ ለማድረግ በማለም የተዘጋጀ መድረክ ነው ።

የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱ በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱ  በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ አበይት የሪፎርም ስራዎች፣ አዲሱን አዋጅ 1333/2016 ተከትሎ የወጡ የህግ ማዕቀፍ ዝግጅትና ማሻሻያ ሥራዎችና የተካተቱ መሠረታዊ ለውጦች፣ የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓቱን ወደ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ከማውረድ ጋር የተያያዙ ተግባራት፣ የተዘጋጁና ጸድቀው ተግባር ላይ የዋሉ መመሪያዎች፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ጥራትና ቅልጥፍናን ለመጨመር የተተገበሩ የዲጅታል ስራዎች በተለይም የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ (ኢጅፒ) ትግበራን ይበልጥ ለማሳለጥ የተሻሻሉ ትግበራዎችና የሲስተሙ ጠቀሜታዎችና አዋጭነት ፣ የቅንጅታዊ አሰራር ውጤታማነትን ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎች፣ የተሠጡ ስልጠናዎችና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች፣ ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተወሰዱ የመፍትሔ አቅጣጫዎችና የተገኙ ውጤቶች በስፋት ተተንትነው ቀርበዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ አያይዘውም የ2018 በጀት ዓመት እቅድን ያቀረቡ ሲሆን እቅዱ የ2017  በጀት ዓመት ክንውንን መነሻ ያደረገና የተገኙ መልካም ውጤቶችን የምናስቀጥልበት በሌላ በኩል የነበሩብንን ክፍተቶች የምንሞላበት እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ሲሉ አብራርተዋል።

በተጨማሪም በኢ.ጂ.ፒ ሲስተም ትግበራ ዙሪያ የተደረጉ ማሻሻያዎች በአቶ እውነቱ አበራ (የኢ.ጂ.ፒ. ሲስተም አልሚና የፔራጎ ሥራ አሰኪያጅ ) የቀረበ ሲሆን ፣ በውስጥ አቅም ለምተው ስራ ላይ የዋሉ ዲጂታል ስራዎች (website, e- learning, letter management, …) በኢጂፒ ፕሮጀክት የአፕሊኬሽን ቲም ባለሞያ አቶ ኃይለሚካኤል ገብሩ አማካኝነት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም የቀረቡትን ገለፃዎችን መነሻ በማድረግ ከመድረክ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ምላሽና ተቋማዊ የማጠቃለያ እና የቀጣይ የጋራ ስራ አቅጣጫዎችና የባለስልጣኑን የመተግበር ዝግጁነት በመግለጽ የዕለቱ መርሃ-ግብር ተጠናቋል።

በ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።


(ሰኔ 13/2017 ዓ.ም)፣ የፌዴራል የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀማቸውን በጋራ ገምግመዋል።

የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱ በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱ  በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ አበይት የሪፎርም ስራዎች፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ጥራትና ቅልጥፍናን ለመጨመር የተተገበሩ የዲጅታል ስራዎች፣ ቅንጅታዊ አሰራር ውጤታማነትን ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎች፣ የሰው ሀይል ግንባታ ላይ የተከናወኑ አበይት ተግባራት፣ ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተወሰዱ የመፍትሔ አቅጣጫዎችና የተገኙ ውጤቶች በስፋት ተተንትነው ቀርበዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ አያይዘውም የ2018 በጀት ዓመት እቅድን ያቀረቡ ሲሆን እቅዱ የ2017  በጀት ዓመት ክንውንን መነሻ ያደረገና የተገኙ መልካም ውጤቶችን የምናስቀጥልበት በሌላ በኩል የነበሩብንን ክፍተቶች የምንሞላበት እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጄ ነው ሲሉ አብራርተዋል።

በተጨማሪም በውስጥ አቅም ለምተው ስራ ላይ የዋሉ ዲጂታል ስራዎች (website, e- learning, letter management, …) በኢጂፒ ፕሮጀክት ባለሞያዎች አማካኝነት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም የቀረቡትን ገለፃዎች መነሻ በማድረግ ከመድረክ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በክብርት ወ/ሮ መሰረት የማጠቃለያ እና የቀጣይ ስራ አቅጣጫ የዕለቱ መርሃ-ግብር ተጠናቋል።

የሴት ሰራተኞች የፎረም አመራርና አባላት የውይይት መድረክ አካሄዱ፡፡

(ሰኔ 7/2017) በቢሾፍቱ ከተማ ፒራሚድ ሆቴል በተዘጋጀው መድረክ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ሴት ሠራተኞች ፎረም አመራር እና አባላት በፎረሙ ህገ-ደንብና በቀሪ ወራት ዕቅድ ዙሪያ ተወያይተው ለተፈጻሚነት ለማጽደቅ ያለመ መድረክ ነው፡፡

በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌን ጨምሮ ሁሉም ሴት ሰራተኞች እና የፎረሙ ተባባሪ አባል የሆኑ ወንድ ሠራተኞች የተሳተፉ ሲሆን የፎረሙን የመመስረቻ ህገ-ደንብ እና የቀሪ ወራት ዕቅድ ለአባላት ቀርበው እና ተወያይተውበት ለግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦች ተነስተዋል፡፡

የተነሱ ሁሉም ግብዓቶች ተካተውበት የተቋቋመበትንም ዓላማ ለማሳካት የሚመጥን ህገ-ደንብ ተዘጋጅቶለት ለአፈጻጸም በሚያመች መልኩ ህገ-ደንብ ማውጣት አስፈላጊ በመሆኑ ለተነሱ ሃሳቦች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶበት እንደሚሻሻል የጋራ ስምምነት ተደርሶበት ህገደንቡም እቅዱም በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡

በመጨረሻም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በንግግራቸው ፎረሙ ሴቶች እርስ በእርስ የሚመካከሩበት፤ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት የሚያጋጥማቸውን እንቅፋቶችም በግልጽ የሚነጋገሩበት ብሎም ነጻ ጊዜ የሚያገኙበት እና ማህበራዊ ግንኙነታቸውን የሚያዳብሩበት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው እና እንደ ተቋምም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዕድል የሚሰጥ ትልቅ ሚናን የሚጫወት በመሆኑ ተቋሙ ሴት ተኮር ስልጠናዎችን፣ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ስራዎችን ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ሠራተኞች ከሚመለከታቸው አደረጃጀቶች ጋር ግንኙነት ፈጥሮ ማመቻቸት እና ቅድመ ስልጠናዎችን ማዘጋጀት፤በጥቅሉ ሴቶች በስነ-ልቦና፤በኢኮኖሚ፤በፈጠራ ችሎታቸው የተሻሉ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ የትኛውንም ተቋማዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመቀጠልም ዋና ዳይሬክተሯ በአስተሳሳብ እና በአመራር ብቃት የተለወጡ መሪዎችን ለማፍራት አጋዥ የሆነውን በሣይንሳዊ ጥናት ተደግፎ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የስራ አመራር እና መሪነት መካከል ያለውን ልዩነት እንዲሁም የመሪነት አስፈላጊነት፤ታሪካዊ የዕድገት ደረጃዎች፤ዘይቤና ክህሎቶች፤ዋና ዋና ተግባራትና መርሆች እንዲሁም ዘመናዊ የአመራር አስተሳሰቦች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ገለጻ ተሰጥቶበታል፡፡

በመጨረሻም ተሳታፊዎች በቀረበው ስልጠና ዙሪያ ሃሳብ አስተያየቶችን በሰፊው በመስጠት የዕለቱን መረሃ- ግብር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡