Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

General

ባለስልጣኑ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የምገባ መርሐግብር አከናወነ።

(ሚያዝያ 04/2018)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራር በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 የተስፋ ብርሃን ምገባ ማዕከል በመገኘት ከ200 በላይ ለሚሆኑ ለአቅመ ደካማ የማሕበረሰብ ክፍሎች ማዕድ በማጋራት የትንሳኤን በዓልን በጋራ አክብረዋል።

በምገባ መርሃግብሩ ላይ በመገኘት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለጹት በዓሉን ስናከብር የሀገር ባለውለታ የሆኑ አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን በማሰብ መሆን እንዳለበት ገልጸው በተለይም እንዲህ አይነት ቦታዎች ላይ በመገኘት ፍቅርንና አንድነትን ማጋራት ያስፈልጋል ብለዋል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት አያይዘውም የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያለውን ጥልቅ ፍቅር ያሳየበት እንደመሆኑ ዕለቱን ተደጋግፎና ተረዳድቶ በማሳለፍ የክርስቶስን ዓላማ ማሳየት እንደሚገባ ያስገነዘቡ ሲሆን እንዲህ አይነት ሰው ተኮር ተግባራት ወደፊትም ተጠናክረው የሚቀጥሉ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

ባለስልጣኑ በአስተዳደራዊ ቅጣት ረቂቅ መመሪያ ላይ ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

(መጋቢት 24/218)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የመንግሥት ግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አስተዳደር ኃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት የሚወሰዱ አስተዳደራዊ ቅጣቶች አፈፃፀም  ረቂቅ መመሪያ ላይ ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች፣ ከግዥና ንብረት ሀላፊዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ መመሪያው የተጠያቂነት መላላትን ለማስቀረት፣ ጠንካራ የህግና የአሰራር ስርዓትን ለመፍጠር እና ብልሹ አሰራርን እንዲወገድ ለማስቻል የተዘጋጀ ሲሆን  በረቂቅ መመሪያው ላይ ግልፅ ውይይትና ግንዛቤ መፍጠር በማስፈለጉ የውይይት መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

የውይይት መነሻ ጽሁፉን ያቀረቡት በገንዘብ ሚኒስቴር የህግ መመሪያ ሀላፊ አቶ ተወዳጅ መሀመድ በበኩላቸው ይህ መመሪያ እንዲወጣ አስቀድሞ በአዋጅ 1333/2016 የተቀመጠ ሲሆን መመሪያው በየደረጃው ያሉ ከግዥና ንብረት ጋር የተገናኙ ሀላፊዎችንና ባለሙያዎችን ሀላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል ብሎም የግዥ አፈጻጸምና ንብረት አስተዳደር ስራው በሀላፊነት እንዲሰራ ለማስቻል የተዘጋጄ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ረቂቅ መመሪያው በማንኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት የተሾመ ወይም የተመደበ ሰው ከግዥ አፈፃፀም እና ንብረት አስተዳደር ጋር በተገናኘ ዓመታዊ የግዥ ዕቅድን፣ የግዥ አፈጻጸም ሪፖርቶችን፣ የንብረት አስተዳደር ሪፖርት በተገቢው የጥራት ደረጃና ግዜ ካላቀረበ እንዲሁም ጥቅም ላይ የማይውሉ እና አገልግሎታቸውን የጨረሱ ንብረቶችን በወቅቱ አለማስወገድ ወይም እንዲወገዱ አለማድረግ እና ሌሌችንም ዝርዝር ጥፋቶችን አካቷል፡፡

ረቂቅ መመሪያው የተዘረዘሩትን ጥፋቶችን ፈፅሞ የተገኘ የስራ ኃላፊና ተሿሚ እንደጥፋት ደረጃውና ድግግሞሹ የተለያዩ ማስጠንቀቂያና የገንዘብ መቀጫ እንደሚጣልበት ያብራራል፡፡

በውይይቱ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን በክብርት ዋና ዳይሬክተሯ እና በሚመለከታቸው የባለስልጣኑ የስራ ሀላፊዎች ምላሽና መብራሪያ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

ባለስልጣኑ በአስተዳደራዊ ቅጣት ረቂቅ መመሪያ ላይ ከፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

(መጋቢት 23/218)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የመንግሥት ግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አስተዳደር ኃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት የሚወሰዱ አስተዳደራዊ ቅጣቶች አፈፃፀም  ረቂቅ መመሪያ ላይ ከፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ከግዥና ንብረት ሀላፊዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ መመሪያው የተጠያቂነት መላላትን ለማስቀረት፣ ጠንካራ የህግና የአሰራር ስርዓትን ለመፍጠር፣ ብልሹ አሰራርን እንዲወገድ ለማድረግ እንዲያስችል ተደረጎ መዘጋጀቱን ተናግረው፤ በረቂቅ መመሪያው ላይ ግልፅ ውይይትና ግንዛቤ መፍጠር በማስፈለጉ የውይይት መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

የውይይት መነሻ ጽሁፉን ያቀረቡት በገንዘብ ሚኒስቴር የህግ መመሪያ ሀላፊ አቶ ተወዳጅ መሀመድ በበኩላቸው ይህ መመሪያ እንዲወጣ አስቀድሞ በአዋጅ 1333/2016 የተቀመጠ ሲሆን መመሪያው በየደረጃው ያሉ ከግዥና ንብረት ጋር የተገናኙ ሀላፊዎችንና ባለሙያዎችን ሀላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል ብሎም የግዥ አፈጻጸምና ንብረት አስተዳደር ስራው በሀላፊነት እንዲሰራ ለማስቻል የተዘጋጄ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ረቂቅ መመሪያው በማንኛውም የመንግስት መ/ቤት የተሾመ ወይም የተመደበ ሰው ከግዥ አፈፃፀም እና ንብረት አስተዳደር ጋር በተገናኘ ዓመታዊ የግዥ ዕቅድን፣ የግዥ አፈጻጸም ሪፖርቶችን፣ የንብረት አስተዳደር ሪፖርት በተገቢው የጥራት ደረጃና ግዜ ካላቀረበ እንዲሁም ጥቅም ላይ የማይውሉ እና አገልግሎታቸውን የጨረሱ ንብረቶችን በወቅቱ አለማስወገድ ወይም እንዲወገዱ አለማድረግ እና ሌሌችንም ዝርዝር ጥፋቶችን አካቷል፡፡

ረቂቅ መመሪያው የተዘረዘሩትን ጥፋቶችን ፈፅሞ የተገኘ የስራ ኃላፊና ተሿሚ እንደጥፋት ደረጃውና ድግግሞሹ የተለያዩ ማስጠንቀቂያና የገንዘብ መቀጫ እንደሚጣልበት ያብራራል፡፡

በውይይቱ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን በክብርት ዋና ዳይሬክተሯ እና በሚመለከታቸው የባለስልጣኑ የስራ ሀላፊዎች ምላሽና መብራሪያ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

ባለስልጣኑ የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸምን ገመገመ፡፡

(መጋቢት 22/2018 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸምን በጋራ ገምገመዋል፡፡

ባለስልጣኑ ከተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ ከመንግስት ግዥና ንብረት ዲጅታላይዜሽን፣ ከዘለቄታዊነት የግዥና /Sustainable Procurement/ ንብረት አስተዳደር ሥርዓት ማጎልበት፣ ከመንግስት ግዥና ንብረት አገልግሎት እና መረጃ ጥራትና ሽፋን ማሳደግ፣ ከመንግስት ግዥና ንብረት የፖሊሲ፣ ማማከር አገልግሎት እና የጥናትና የምርምር፣ ከመፈፀምና ማስፈፀም አቅም ግንባታ፣ ሙያዊ ድጋፍ፣ ክትትል የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ከመስጠት፣ ከስትራቴጂያዊ የቴክኒክ ትብብር እና አጋርነትን ከማጠናከር፣ ከመንግስት ግዥና ንብረት ኦዲትና ክትትል ሥራዎችን ጥራትና ሽፋን ከማሳደግ እንዲሁም ከግዥ አፈፃፀም እና ንብረት ሽያጭ ላይ የሚቀርቡ የይግባኝና የጥፋተኝነት ውሳኔ አሰጣጥን ከማጠናከር አንጻር የተቋሙን አፈጻጸም በጥልቀት ገምግሞ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

ባለስልጣኑ የአሰራር ስርዓቱን ጥራትና ቅልጥፍና ለማሳደግ አዋጁን ጨምሮ መመሪያዎችንና ሌሎች የአሰራር ስርዓቶችን ውጤታማ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን ከዲጂታላይዜሽን አንጻርም የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP)፣ የተሸከርካሪ ስምሪት፣ ነዳጅ አጠቃቀም ሥርዓት (Fleet Management System)፣ የበየነ መረብ ትምህርት (e- learning) እና ሌሎች ዲጂታል አገልግሎቶችን እየተገበረ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

ተቋሙ በትኩረት እየተገበራቸው ከሚገኙ አበይት ዲጂታል ተግባራት አንዱ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥን (e-GP) ወደ ክልሎች ማውረድ መሆኑንና ቀድመው የጀመሩትን አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደርና ኦሮሚያ ክልልን ከመደገፍ በተጨማሪ ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ለሶማሌ ክልል፣ ለአማራ ክልል እና ለድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር ስርዓቱን ሊተገብሩ በሚችሉብት ሁኔታ ላይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እና የቴክኒክ ድጋፍ መሰጠቱም ተብራርቷል፡፡

በሪፖርቱ ከተብራሩና ተቋሙ በትኩረት ከሚያከናውናቸው አበይት ተግባራት አንዱ የኦዲት ስራ ሲሆን በ9 ወራት በ56 ተቋማት ላይ የህጋዊነት ኦዲት (93.3%)፣ በ38 ተቋማት ላይ የክትትል ስራ (100%)፣ በ13 ተቋማት ላይ የጥቆማ ኦዲት (100%) እንደተከናወነ በሪፖርቱ ተካትቷል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ይግባኝና ጥፋተኝነትን በሚመለከት በ9 ወራት ውስጥ 174 የጥፋተኝነት ሪፖርት መረጃ ተሟልቶላቸው ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የቀረቡ ሲሆን 167 (95.97%) ውሳኔ እንዲያገኙ ተደርጓል:: በሌላ በኩል ይግባኝን በሚመለከት በ9 ወራት ውስጥ መረጃ ተሟልቶላቸው ከቀረቡ 101 ይግባኝ ውስጥ 98 (97%) ውሳኔ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

በመጨረሻም የሪፎርም ስራዎችን አጠንክሮ ማስቀጠል፣ የድጋፍና ስልጠና ስራዎችን ማጠናከር፣ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥን ወደ ክልሎች ለማውረድ ተጨማሪ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ በዋና ዳይሬክተሯ ክብርት ወ/ሮ መሰረት አቅጣጫ ተቀምጦ ግምገማው ተጠናቋል፡፡