Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

News

Federal Public Procurement and Property Authority shared it best practices on Electronic Government Procurement system.

(7 sep. 2026| Addis Ababa) — The Federal Public Procurement and Property Authority (FPPPA) hosted a delegation from the Public Procurement Authority of Nigeria for a high-level peer-to-peer knowledge exchange focused on Electronic Government Procurement (e-GP) systems.

FPPPA Director General, H. E. Mrs. Meseret Meskele, welcomed the delegates and delivered the opening address, highlighting the current situation and overall strategic direction of Ethiopia’s public procurement and property management systems. Emphasizing that digital transformation goes beyond digitizing procedures, she framed technology as a vital tool to strengthen transparency, efficiency, and accountability.

She also emphasized that one of the important areas of our e-GP development is integration of the procurement system with other government digital platforms and Such integration is essential for creating a connected government ecosystem, reducing duplication, improving data exchange, and making public services more efficient.

H.E. incorporate that sharing knowledge, experiences, innovations, and practical solutions with African brothers’ is more crucial to improve gaps and to become more efficient and competent.

During the session, Mr. Yafet Mekonnen, e-GP Project Manager, delivered a comprehensive presentation detailing the operational rollout and execution overview of Ethiopia’s e-GP system. At the discussion, the Nigerian delegation raised technical and strategic questions regarding implementation strategies, to which FPPPA officials provided clarifications.  

የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን በዲጂታል የመረጃት ስስር ላይ ምክክር አካሄዱ።

(ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም|አዲስ አበባ)፡ የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ከግንባታ ባለሙያዎች፣ ኩባንያዎች እና ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የመረጃ ልውውጥና ትስስር መፍጠር በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ የጋራ የምክክር መድረክ አካሂደዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር) እንዲሁም የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ጋር በመተባበር ያበለጸገው «ዲጂታል የኮንስትራክሽን ሬጉላቶሪ ኢንፎርሜሽን ሲስተም» (Construction Regulatory Information System) ይዘት እና ሞጁሎች ላይ ገለጻ ቀርቦ ከመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስር ዓት ጋር መተሳሰር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጎበታል።

የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ተቋማቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው የመረጃ ትስስር ማድረጋቸው የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ ዲጂታል ለማድረግ የሚደረገውን ጉዞ ከማፋጥን እንዲሁም የተገልጋዮችን አላስፈላጊ ወጪና እንግልት ከመቀነስ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚኖረው ከመሆኑም በላይ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውልና የግንባታ ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ያስችላል ብለዋል።

ሁለቱ ተቋማት በተለይም በዲጂታል ሥርዓት ደረጃ ሊለዋወጧቸው የሚገቡ አስፈላጊ፣ ወቅታዊና ተዓማኒ መረጃዎች ላይ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን በቀጣይም በጋራ የሥራ ሂደት የመረጃ ልውውጥ ሥርዓቱን ይበልጥ ለማዳበርና ለማጠናከር ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን  የመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓቱን (e-GP) ከተለያዩ የመንግሥትና የቁጥጥር ተቋማት ዲጂታል ሲስተሞች ጋር በማስተሳሰር የአገልግሎት ጥራትንና ግልጽነትን ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን የሴት ሰራተኞች ፎረም ዓመታዊ ጉባኤውን አካሄደ::

(ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም| አዲስ አበባ) — የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን የሴት ሰራተኞች ፎረም የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም. የሥራ አቅጣጫ ማስቀመጫ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በድምቀት አካሂዷል።

 

በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ባደረጉት ንግግር የሴት ሰራተኞች ተሳትፎ በዘመናዊ ተቋም ውስጥ ተጨማሪ ጉዳይ ሳይሆን የተቋሙ የልማትና የስኬት ዋና አካል መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም ሴቶች በሙያቸው ብቻ ሳይሆን በአመራርነት፣ በውሳኔ አሰጣጥ፣ በፈጠራና በተቋማዊ ለውጥ አስተዳደር ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

 

ክብርት ወ/ሮ መሰረት አያይዘውም በተለይም ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎች፣ የዲጂታል ሥርዓት ዝርጋታዎችና የሰው ኃይል አቅም ግንባታ በሚከናወኑበት ወቅት የሴቶች ሙሉ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም የሴት ሰራተኞችን የሙያና የአመራር አቅም ለማሳደግ ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ሙሉ ቁርጠኝነት ያለው መሆኑን አረጋግጠዋል።

ፎረሙ በ2019 በጀት ዓመትም የሴት ሰራተኞችን የሙያና የአመራር አቅም ማሳደግ፣ በውሳኔ አሰጣጥና በአመራር ደረጃ የሚኖራቸውን ተሳትፎ ማጎልበት እና  ፍትሃዊ የሥራ አካባቢንና የሥልጠና/ኮቺንግ እድሎችን ማጠናከር ላይ በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅበት ተቁመዋል።  

በመድረኩ ላይ የፎረሙ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በወ/ሮ ሰናይት አንበሴ ቀርቦ በተገኙት ውጤቶች፣ በተለዩ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች እና በ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

 ከፎረሙ ዓመታዊ ውይይት ጎን ለጎን በባለስልጣኑ የቀን ማቆያ ቆይታቸውን አጠናቅቀው ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ለሚገቡ ሕፃናት የሽኝት መርሃ-ግብር የተካሄደ ሲሆን ለሕፃናቱ የመማሪያ ቁሳቁስ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። ይህ ድጋፍ ሰራተኞች የቤተሰብና የሥራ ኃላፊነታቸውን አጣጥመው እንዲወጡ ከተደረጉ ተቋማዊ ድጋፎች መካከል አንዱ ማሳያ መሆኑ ተመልክቷል።

ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

(ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም) — የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትንና ቅልጥፍናን ለማሳደግ እንዲሁም የዲጂታል አሰራርን ተደራሽነት ለማስፋት የሚያስችለውን ታሪካዊ የሁለትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ተፈራረመ።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍናን ለማረጋገጥ፣ አሰራሮችን ለማዘመን እና የመንግስት ሀብትና ገንዘብ የሚገባውን ተገቢ ዋጋ (Value for Money) እንዲያስገኝ ለማስቻል ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን በከፍተኛ ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት በማከናውን ላይ ይገኛል። ከእነዚህም ዋና ዋና ስራዎች መካከል  የመንግስት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትን (e-GP system) በስፋት መተግበር አንዱ ሲሆን ባለስልጣኑ ስርዓቱን በሁሉም የፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ እንዲውል አድርጓል። በአሁኑ ወቅትም ይህንን ዘመናዊ አሰራር ቀድመው የጀመሩትን አዲዝ አበባ ከተማ መስተዳደርና እና ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ ወደ ሌሎች ክልሎ ለማውረድ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል።

የመግባቢያ ሰነዱን የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ሚዴቅሳ ቶሎሳ በጋራ ተፈራርመውታል።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለጹት ባለስልጣኑ የአሰራር ስርዓቱን በማዘመን የህዝብና የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በተነሳሽነት እየሰራ ይገኛል። ባለስልጣኑ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣትና የጀመራቸውን የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ግብ ለማድረስ ከስልታዊ አጋር ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።

አክለውም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገሪቱ ሰፊ የደንበኞች ቁጥርና አጠቃላይ ተደራሽነት ያለው ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም በመሆኑ ከባንኩ ጋር አብሮ መስራት የባለስልጣኑን ተገልጋዮች ከተንዛዛ እንግልት ለመታደግና ባሉበት ቦታ ሆነው ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ሚዴቅሳ ቶሎሳ በበኩላቸው ባንኩ ሰፊ የቴክኖሎጂ ሽፋንና ዘመናዊ የዲጂታል ባንኪንግ መሰረተ-ልማት ያለው መሆኑን አብራርተዋል። በተጨማሪም ባንኩ ከበርካታ የመንግስትና የካምፓኒ ተቋማት ጋር በጥምረትና በቅንጅት የመስራት የካበተ ልምድ እንዳለው ያወሱት ምክትል ፕሬዘዳንቱ ከመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ጋር ተቀናጅቶ መስራት ለባንኩ ተጨማሪ እሴት የሚፈጥርለት መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህ የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ የባንኩን የዲጂታል ክፍያና የፋይናንስ አገልግሎት ከኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ ስርዓት (e-GP) ጋር በማስተሳሰር የግዥ ሂደቱን የበለጠ ግልጽ፣ ፈጣን እና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።