Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

ድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር በቅርብ ቀን የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥን (e-GP) ተግባር ላይ እንደሚያውል ተገለጸ።

(ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥን (e-GP) መተግበር በሚችልበት ሁኔታ ላይ ከድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር ጋር ውይይት አድርጓል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስቀድሞ ለከተማ መስተዳደሩ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ አፈጻጸም እንዲሁም ከአዋጅና ከመመሪያዎች ጋር ተያይዞ ስለሚፈጠሩ ለውጦች ተከታታይ ስልጠናዎች ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር የግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅና መምሪያ ከልሶ ወደ ስራ ለመግባት ከባለስልጣኑ ጋር ውይይት አድርጓል።

በእለቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለጹት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይ እያደረገ ነው ብለዋል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በተለይም ባለስልጣኑ የግዥ ሂድቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ዋጋ እንዲያስገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ስራ እየተሰራ መሆኑን ያብራሩ ሲሆን በተለይም የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት የግዥ ሂደቱን ከእጅ ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ ተደራሽነትን በማስፋት፣ አሳታፊነትን በመጨመር፣ ወጪን በመቀነስ እና ግልጸኝነትን በማስፈን ረገድ ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑን አመላክተዋል።

በሌላ በኩል የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ አተገባበርን፣ ዓላማ፣ ተጠቃሚ እና አጠቃላይ ይዘትና ሂደትን በሚመለከት በኢጂፒ ፕሮጀክት የቴክኖሎጂ ዘርፍ ም/ማናጀር አቶ ያፌት መኮንን ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በመጨረሻም ስርዓቱን በውጤታማነት ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከመጡ ባለሙያዎች ቀርቦ ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን ከተማ መስተዳደሩ በአጭር ጊዜ የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ  ግዥ ስርዓትን እንደሚተገብርም አንስተዋል። በሌላ በኩል ለትግበራው ባለስልጣኑ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት ገልጸዋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *