Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በባለስልጣኑ የአሰራር ስርዓትና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የመስክ ምልከታና ግምገማ አካሄደ

(ሰኔ 27/2018 ዓ.ም)፣ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን የአሰራር ስርዓት እና የዲጂታልና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለመገምገም የሚያስችለውን የመስክ ምልከታና የሰነድ ምርመራ አካሂዷል።

የግምገማ መድረኩን የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሚኒሊክ ሳሙኤል በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱ ሲሆን፣ ባለስልጣኑ የአገልግሎት አሰጣጡን ጥራት፣ ተደራሽነትና ቅልጥፍና ይበልጥ ለማዘመን በርካታ ስትራቴጂካዊና ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን በትጋት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አያይዘውም የጥራት ሽልማት ድርጅቱ የገምጋሚ ኮሚቴ አባላት የሚሰጧቸው ገንቢ አስተያየቶችና ግብረ-መልሶች የተቋሙን የሪፎርም ጉዞ ይበልጥ ለማቀጣጠልና ለወደፊት ስራዎች እንደ ትልቅ መስፈንጠሪያ (Springboard) ሆነው እንደሚያገለግሉ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ የአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍናን ለመጨመርና አሰራሩን ለማዘመን (በተለይም በቴክኖሎጂ የታገዙ ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን) ማከናወኑ የሚታወቅና ለሽልማት ድርጅቱም በሰነድ ያሳወቀ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ እነዚህ የተከናወኑ ተስፋ ሰጪ ስራዎች ተቋማዊ ስርዓት የተበጀላቸው፣ ቀጣይነት ያላቸውና መሬት ላይ በግልጽ የሚታዩ መሆናቸውን በጥራት ሽልማት ገምጋሚ ኮሚቴው ማረጋገጥ እንደሚገባና ዋናው የሂደቱ ዓላማም ይሄው መሆኑን አስረድተዋል።

የጥራት ሽልማት ኮሚቴ አባላትም ባለስልጣኑ በተለያዩ ቁልፍ የተቋማዊ ብቃት መስፈርቶች ላይ ያለውን ልምድና አደረጃጀት በጥልቀት መዝነዋል። በተለይም የአሰራር ስርዓት ግንባታና ተቋማዊ ባህል፣ የውስጥና የውጭ ቅንጅታዊ አሰራር እንዲሁም ተግባቦት (Communications)፣ የሰራተኞች አያያዝ፣ የስራ አካባቢ ምቹነትና የማበረታቻ (ማትጊያ) ስርዓቶች፣ የተገልጋይ አያያዝ፣ ቅሬታ አፈታትና የደንበኞች ግንኙነት፣ የማህበራዊ ኃላፊነት (CSR) አፈጻጸም እና መሰል መመዘኛዎች ላይ ትኩረት አድርገዋል።

ከመስክ ምልከታው በኋላ ገምጋሚ ኮሚቴ ምልከታውን ያቀረበ ሲሆን የመስክ ምልከታና የባለሙያዎች ግምገማ ከውድድሩና ከጥራት ሽልማቱ ባለፈ ባለስልጣኑ በአሁኑ ወቅት የያዘውን ዘመናዊ ጥራትና ቅልጥፍናን መሰረት ያደረገ የሪፎርም ጉዞ የሚያጠናክርና ለተቋሙ ቀጣይ እድገት ትልቅ ተጨማሪ እሴት (Value Addition) የሚፈጥር መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ገልጸዋልል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *