Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

 የመንግሥትኤሌክትሮኒክግዥሥርዓትግልፀኝነትንበመፍጠርየሙስናተጋላጭነትንይቀንሳል›› – አቶ አዲስ ጎዳና

የኢፌዴሪ የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን የተሰጡትን ኃላፊነትና ተግባር ለማከናወን እያደረገ የሚገኘውን እንቅስቃሴ በዚህ ዓምድ ላይ በማቅረብ አንባቢዎች ስለ ባለሥልጣኑ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እየተደረገ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረት በባለፈው ዕትም ስለ ዘላቂ የመንግሥት ግዥ ምንነት፣ ዓላማዎች፣ መርሆዎች፣ አተገባበር እና ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ ምን መደረግ እንዳለበት በመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ከሆኑት ከአቶ ዮናስ ሀበሻ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ አቅርበን ማስነበባችን የሚታወስ ነው፡፡

በዛሬው ዓምዳችን ደግሞ የኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ሥርዓት የሕጋዊነት ኦዲት እና የኦዲት ክትትል ሚናን በሚመለከት ከክዋኔና ሕጋዊነት ኦዲት ክትትል ሥራ ክፍል መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አዲስ ጎዳና ጋር ቆይታ በማድረግ ምላሻቸውን ይዘን ቀርበናል፡፡

በቅድሚያ የክዋኔና ሕጋዊነት ኦዲት ክትትል ሥራ ክፍልን ተልዕኮ እና ኃላፊነት ቢያብራሩልን ?

አቶ አዲስ:- ጥያቄውን ከመመለሴ በፊት መነሻ ማድረግ የሚያስፈልገው ጉዳይ አለ፡፡ ይኸውም የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 13 ምን ይላል የሚለውን ማየት አስፈላጊ ይሆናል። በዚህ አዋጅ አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ 13 የመንግሥት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር እንዲሁም የመንግሥት እና የግል አጋርነት ዘርፍ ግዥዎችን አፈፃፀም በራሱ ዕቅድ፣ እንዲሁም ጥፋት ስለመፈፀሙ ጥቆማ ሲቀርብለት ሂደቱን በማስቆም የሥርዓት መጠበቅ ወይም የክዋኔ ኦዲትና ክትትል የማካሄድ እና በግኝቱ መሠረት ተገቢውን ርምጃ እንደ አግባብነቱ በራሱ መውሰድ ወይም ሥልጣን ባላቸው ሌሎች አካላት እንዲወሰድ ማድረግ መሆኑን ያስቀምጣል።

ይህን መነሻ አድርገን የክፍሉን ሥራ ስንመለከት የክዋኔና ሕጋዊነት ኦዲት ክትትል ሥራ ክፍል በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የሚፈጸሙ ተግባራት ከሕግ፣ ከደንብ፣ ከመመሪያ እና ከተቀመጡ አሠራሮች ጋር ተጣጥመው መፈጸማቸውን ለማረጋገጥ የሚሠራ ክፍል ነው።

በተጨማሪም የኦዲት ግኝቶችና ምክረ ሀሳቦች በተገልጋይ ተቋማት ተግባራዊ መደረጋቸውን በመከታተል የአሠራር ክፍተቶች እንዲታረሙ እና የተቋማት የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት እንዲጠናከር ያግዛል። በመሆኑም ክፍላችን በመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውስጥ የተጠያቂነትና የግልፅነት ባሕል እንዲጎለብት ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *