Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

አብሮ መስራት የሚያስችል ውይይት ተካሄደ።

(ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአሰራር ስርዓቱን በማዘመንና ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ዋጋ እንዲያስገኝ ለማስቻል ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ከማድረግ ጀምሮ ያልተቋረጥ ስልጠና፣ ድጋፍና ክትትል እያደረገ ይገኛል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በየተቋማቱ ከሚሰጠው ስልጠና በተጨማሪ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቭርሲቲ ስልጠና ሊሰጥ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ከዩኒቭርሲቲው አመራር ጋር ውይይት አድርጓል።

ከውይይቱ በተጨማሪ በባለስልጣኑ አመራር የስልጠና እና የዲጂታል ላይብራሪ ጉብኝት የተካሄደ ሲሆን ባለስልጣኑ የያዘውን የዲጂታል ግዥና ንብረት ስራ የሚያግዝ እና ለሰልጣኞችም ምቹ መሆኑም በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *