ባለስልጣኑ የግዥ ባለሙያዎች በሚሰጥበት ስልጠና ላይ ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አመራር ጋር ውይይት አደረገ።

(ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የተቋማት ግዥ ባለሙያዎችን አቅም አጎልብቶ የግዥና ንብረት ጥራትና ቅልጥፍናን ለመጨመር እና የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ዋጋ እንዲያስገኝ የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የግዥና ንብረት ባለሙያዎችን አቅም ለማጎልበት አጫጭር ስልጠናዎችን እና ድጋፎችን እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨስሪቲ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት በፈጸመው መሰረት በቅርብ በሚጀምሩት የስልጠና ይዘቶች፣ አሰልጣኞች፣ የስልጠና ሁኔታ እና ስለ ሰልጣኝ የግዥና ንብረት ባለሙያዎች ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ማስጀመሪያ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ደረጄ እንግዳ (ዶ/ር) እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከግዥና ንብረት ባለስልጣን ጋር አብሮ በመስራቱ ደስተኛ እንደሆነና ውጤታማ ስራዎችን እንደምንሰራ አምናለሁ ብለዋል።
በሌላ በኩል የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤት በአዋጀ ከተሰጡት ተግባራት አንዱ ለግዥና ንብረት ባለሙያዎች የፕሮፌሽናላይዜሽን ስልጠና መስጠት በመሆኑ ይህን ስልጠና ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማስኬድ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተመራጭ ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል።
በእለቱ መሰረታዊ የሙያዊ ስልጠና (Basic Level Professionalism Training) እና የሥርዓተ-ትምህርት ይዘት እና የብቃት ማዕቀፍ (curriculum syllables and competency framework) ሰነዶች ለዩኒቨርሲቲው አመራር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
ከገለጻው በኋላ ከዪኒቨርሲቲ አመራሮች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን በባለስልጣኑ አመራርና ባለሙያዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
በእለቱ ከግዥናን ንብረት ባለስልጣን ባለሙያዎች ገለጻ በተጨማሪ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቭርሲቲ አበርክቶት ለውይይት ቀርቧል። የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡ ዶ/ር አከሊሉ ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ በተጨማሪ በጥናትና ምርምር፣ በማማከርና በካሪኩለም ቀረጻ ከፍተኛ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ያብራሩ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው በሙሉ አቅሙ ለማገዝ ፈቃደኛ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመጨረሻም አዲስ አበባ ሳይንስና ቲክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ጥናቶችን በመስራት፣ በማማከርና በማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች አቅም ያለው ተቋም በመሆኑ ውጤታማ ስራዎችን እንደምንሰራ ተስፋ አደርጋለሁ፤ ለዚህም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ያሳየውን የማገዝና አብሮ የመስራት ፍላጎት አደንቃለሁ ሲሉ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።












0 Comments