ባለስልጣኑእያከናወናቸውየሚገኙትየሪፎርምሥራዎችበባለስልጣኑየአገልግሎትአሰጣጥጥራትናቅልጥፍናላይያመጡትተጨባጭለውጥአለብለውያምናሉ? ቢያብራሩልን።
አቶ ዳንኤል ፦ በሚገባ አምናለሁ፡፡ የሪፎርም ሥራዎች በባለስልጣኑ አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍና ላይ ተጨባጭ ለዉጥ አምጥተዋል ስል ቀደም ሲል ለሙያዊ ምክር፣ ለስልጠና ጥያቄዎች፣ ለቴክኒካዊ ድጋፍ በተለይ ኢጂፒ አጠቃቀም ላይ ወደ ተቋማችን የሚመጡ ተቋማትም ሆነ የንግዱ ማህበረሰብ ማናቸዉንም አገልግሎቶች ባሉበት ሆነዉ በተዘረጋዉ ዲጅታል አሠራር አገልግሎቶችን እንዲያገኙ በማድረግ ሊወጣ የሚችለዉን የጊዜ፣ የጉልበት፣ እና የገንዘብ ወጪ ማስቀረት ተችሏል፡፡
በተጨማሪም ኤሌክትሮኒክ ትምህርትን በመጠቀም የስልጠና እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች በመከናወናቸዉ ተገልጋዮች ባሉበት ሆነዉ ተቋሙን እንዲያዉቁትና ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎት እንዲረዱ ማድረግ አስችሏል ብሎ መዉሰድ ይቻላል፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን እንደ ምሳሌ አነሳን እንጂ ሁሉም የሪፎርም ተግባራት በባለስልጣኑ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍና ላይ ከፍ ያለ አስተዋጽዖ አበርክተዋል ብለን ማስቀመጥ እንችላለን፡፡

0 Comments