Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

Author: Yonas Habesha

Discussion were held with UNOPS Procurement Advisor

(October 13/2025), The Federal Government Procurement and Property Authority is an institution that is working diligently to strengthen a modern government procurement and Property system and become one of the leading institutions in Africa by 2028. The authority has been able to digitalize operations to realize this vision, and fulfill its assigned responsibilities with high efficiency and increase the quality of service.
In particular, it has been given extensive functions and responsibilities under Proclamation 1333/2024, and it has been prepared guidelines and operating systems to carry out these functions and responsibilities, including Standard Ben Documents and Life Cost Analysis Documents. Therefore, the institution held discussions with UNOPS Procurement Advisor James Landels to improve the quality of the Life Costing Analysis document it is currently preparing. During the discussion, the content of the Life Costing Guidance document and UNOPS’s life-cycle costing guidance, as well as the overall procurement policy, were reflected for further discussion. In the discussion, to enhance the quality of the LCA document being prepared by the PPA, procurement experiences from various countries were presented by James, and discussions were held on the preliminary preparations and documents that should be prepared to ensure sustainable procurement.

ባለስልጣኑ የሰንደቅአላማን ቀን በድምቀት አከበረ።

(ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም) የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘውን የሰንደቅ አላማ ቀን ከእቅድና ፕላን ሚኒስቴር እንዲሁም ከመንግስት ግዥ አገልግሎት ጋር በመሆን በድምቅት አክብሯል።

የሰንደቅ ዓላማ ቀን ዘንድሮ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን  ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ማንሰራራት አዲስ ዘምን ድል ብሥራት፣ የኅብረብሔራዊነታችን እና የአብሮነታችን የታሪክ ማብሰሪያ ዓርማ፣ ለኢትዮጵያ ሕዳሴ፣ የጀግንነታችንና የአያበገሬነታችን መገለጫ፣ የነፃነታችን ማማ፣ ለኢትዮጵያ ዐዲስ ዘመን ከፍታ፣ የዘመናት የነጻነታችንና የሥልጣኔያችን አብሪ ኮከብ፣ የሕዳሴያችን ሕያዊ ምስክር፣ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነታችን መገለጫ፤ የሀገራችን ታላቅነት ማብሰራያ፣ የብልፅግናችንና የሐገራዊ ከፍታችን ብርሃን ማሳያ፣ ለጠንካራ ሀገር መንግስት ግንባታ፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ ቆራጥ አመራር ፈተናዎችን አሸንፋ ትሻገራለች በሚሉ መልዕክቶች ደምቆ እየተከበረ ይገኛል።

ባለስልጣኑ ከክልል ግዥና ንብረት ተቆጣጣሪ አካላት፣ ከመንገድ ሴክተር የክልል ቢሮ ሀላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት አካሄደ።

(መስከረም 29/2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የግዥ ጥራትና ቅልጥፍናን ለማረጋገጥ በየደረጃው ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው እለት ከክልል ግዥና ንብረት ተቆጣጣሪ አካላት እና ከመንገድ ሴክተር የክልል ቢሮ ሀላፊዎች ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለጹት ውይይቱ ቁልፍ የግዥ አመላካቾች እና የግዥ ኦዲት ላይ ተወያይቶ የጋራ መግባባት መድረስ መሆኑን አመላክተዋል። ክብርት ወ/ሮ መሰረት በንግግራቸው የገጠር መንገድና መሰረተ ልማት ከፍተኛ በጀት የሚጠይቅ እና የሚዘረጋው የገጠር መንገድና መሰረተ ልማት ጥራትና ታማኝነትን ያማከሉ እንዲሆኑ ከቁልፍ የግዥ ሂደቶች በተጨማሪ ኦዲት መደረግ ያለበት በመሆኑ የግንዛቤ ማስጨባጫ መድረኩ እንደተዘጋጄ አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የመጀመሪያውን ገላጻ ያቀረቡት  በከተማና መሰረት ልማት ሚኒስቴር የገጠር ልማትና ትሥስር ፕሮግራም ማናጀር አቶ መሃመድ አሚን ሲሆኑ በዋናነት የገጠር መሰረተ ልማት የማህበረሰብን ተሥስር በመፈጠር፣ የንግድ ትሥስርን በመፍጠር፣ ጤና ጣቢያዎች እና ትምህርት ቤቶች ከማህበረሰቡ እንዲገናኙ በማድረግ በኩል የጎላ ሚና ያለውና ከፍተኛ በጀት የሚበጀትለት በመሆኑ በህግ መመራት ብሎም የኦዲት ክትትል መደረግ ይኖርበታል። ለዚህ ደግሞ የክልል አመራሮች ሚናቸው የጎላ በመሆኑ ውይይቶችን ማድረግና በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብልዋል።

በቁል የግዥ መለኪያዎች ላይ ገለጻ ያቀረቡት በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከፍተኛ የፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ጸጋዬ አበበ በበኩላቸው ቁልፍ የግዥ መለኪያዎች የግዥ መርሆቻችን በትክክል መተግበራቸውን የምናይበትና የምንለካበት መከታተያ መሳሪያ በመሆኑ የሚፈጸመው ግዥ ቁልፍ የግዥ መለኪያዎችን ያሟላ መሆን ይኖርብታል ሲሉ አብራርተዋል።

በእልቱ የግዥ ኦዲትን በሚመለከት በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የክዋኔና የህጋዊነት ኦዲት ክትትል መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ አዲስ ጎዳና ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። አቶ አዲስ በገለጻቸው ኦዲተሮች የተቋም መሪዎች አጋዥ በመሆናቸው መሪዎች ሊደግፏቸውና በመርህ እንዲመራ ማድረግ ይኖርባቸዋል ሲሉ አሳስበዋል።

ገለጻዎችን ተከትሎ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን ከተሳታፊዎች የተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

የኤሌክትሮኒክ የመንግሥት ግዥ ስርዓት በግዥ ሂደት ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን ነው፦ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን

(መስከረም 08/2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) በሚተገበርበት ሁኔታ ላይ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ ወቅት ባለስልጣኑ የግዥ ሂድቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ዋጋ እንዲያስገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ስራ እየተሰራ መሆኑን የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ አብራርተዋል። ክብርት ወ/ሮ መሰረት አያይዘውም የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት የግዥ ሂደቱን ከእጅ ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ ተደራሽነትን በማስፋት፣ አሳታፊነትን በመጨመር፣ ወጪን በመቀነስ እና ግልጸኝነትን በማስፈን በኩል ያለው አስተዋጽዖ ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት በገለጻቸው ሁሉም የፌዴራል መስሪያ ቤቶችና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ግዣቸውን በዚህ ስርዓት እየፈጸሙ የሚገኙ ሲሆን አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደርና ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ ስድስት ክልሎች ወደ ትገበራ እየገቡ እንደሚገኙ እንዲሁም ሌሎች ክልሎችም ስርዓቱን እንዲተገብሩት ለማስቻል ተከታታይ ውይይቶች እየተደረገና ስልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ስርዓት በግዥ ሂደት ውስጥ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን ስርዓት ነው ሲሉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገልጸዋል። ‎

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን መንግሥት በተቋማት ሪፎርም ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው በግዥ ስርዓቱ እየተደረገ ያለው ሪፎርም አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አያይዘውም ‎የግዥ ስርዓቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ በግዥ ሂደት ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚገባ የተናገሩ ሲሆን የክልሉ መንግሥት የኤሌክትሮኒክ የመንግሥት ግዥ ስርዓት ለመተግበር ቁርጠኛ መሆኑንና ለዚሁ የሚያግዝ አዋጅ መጽደቁን አመላክተዋል።

በመጨረሻም ስርዓቱን ተግብሮ ለማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከተሳታፊዎች አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን ክልሉ ወደ ኤሌክትሮኒክ የመንግሥት ግዥ ስርዓት ለመግባት በሚያደረገው ጥረት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ድጋፉን እንዲያጠናክርም ርዕሰ መስተዳደሩ አሳስበዋል።