ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራር ጋር ውይይት እያደረገ ነው።

(ጥር 02/2018 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥን ንብረት ባለስልጣን ከኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢዎች፣ ከፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ከአማካሪ ኮሚቴ አመራር እና ከምክር ቤቱ ሴቶች ኮከስ አመራሮች ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል።
ውይይቱ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን እያከናወናቸው በሚገኙ ክንውኖች፣ የዲጂታል ስራዎች፣ የግዥና ንብረት የህግ ማዕቀፎች እና ወደፊት በትኩረት ሊሰራባቸው በታቀዱ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።




0 Comments