Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

News

በፌደራል የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዐዋጅ ቁጥር 1333/2016 በተካተቱ አዳዲስ ይዘቶችና የተሻሻሉ ጉዳዮች ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

(ግንቦት 10/2017ዓ/ም) የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 1333/2016 የጸደቀውን አዲሡን አዋጅ ማስፈጸም የሚያስችሉ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያወችን እያዘጋጀ የቆየና ቀደም ሲል የራሱን ሠራተኞች ጨምሮ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት እያወያየ ገንቢ አሥተያየቶችን በማሻሻያነት እየጨመረ አዋጁን ለሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት በማስገምገም ግብዓት በማሰባሠብ አበልጽጎ የማስፈጸሚያ መመሪያዎችን አዘጋጅቷል።

ስለሆነም የተናበበና የተጣጣመ የግዥና ንብረት አስተዳደር ስርዓት እንዲኖር ሁሉም ክልሎች አዋጁን መሠረት ያደረገ መመሪያ አዘጋጅተው የአካባቢያቸውን ተጨባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት መሠረታዊ ህጉንና የአሠራር ሥርዓቱን ሳያዛቡ አዘጋጅተው እንዲተገብሩ እንደሚረዳ ታሥቦ መመሪያውን ከሚቀዱበት አዋጅ አኳያ የተካተቱ አዳዲስ ይዘቶችንና የተሻሻሉ ጉዳዮችን ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ለክልልና የከተማ መስተዳድር ቢሮ ኃላፊዎች በደብረ ዘይት ከተማ ፒራሚድ ሆቴልና ሪዞርት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነው።

በዐዋጁ የተካተቱ አዳዲስ ይዘቶችና የተሻሻሉ ጉዳዮች የመንግስት ግዥ ማሻሻያ አቅም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ በሆኑት አቶ መላኩ ተጓዴ የቀረበ ሲሆን በዋናነት አዲሡ አዋጅ ከነባሩ ያለውን ጉልህ ልዩነት በማሳየትና የተደረጉ መሠረታዊ ማሻሻያዎችና የተካተቱ አዳዲስ ይዘቶች ላይ ልዩ ትኩረቱን ያደረገ ማብራሪያ ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።

መሪ ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ክልሎች ከአዋጁ ጋር የተናበበና የተቀራረበ የማስፈጸሚያ መመሪያቸውን ሲያዘጋጁ ሀገራዊ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ የማስፈጸሚያ ህጎችን ባስጠበቀ መልኩ ስለሚሆን ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አጣጥመው መመሪያ አዘጋጅተው ለመፈጸም እንዲችሉ ስለሚረዳ የተሻሻሉ እና እንደ አዲስ የተካተቱ ይዘቶችን ልዩ ትኩረት ሠጥቶ
መረዳቱ አስፈላጊ መሆኑንን ተገንዝበው ሊሻሻል ይገባል በሚሉት ዙሪያም ሀሳብ አስተያየታቸውን ለተጨማሪ ግብዓትነት ሊሠጡ እንደሚገባ በገለጻቸው ወቅት አሳስበዋል።

በመቀጠልም ተሳታፊዎች ባለሥልጣኑ እየተገበረ ያለው መሠረታዊ ተግባሮች በቂ ዝግጅት የተደረገበትና ሀገሪቱን የሚመጥን
መሆኑን በአድናቆት በመግለጽ፤
ከህይወት ዘመን ወጭ ትንተና፣ከግልግል ዳኝነት፣ከቀጥታ ግዥ ፣ ከክዋኔ ኦዲት ጋርስ ተያያዥነነት ያላቸውና ሌሎች መሠል ጉዳዮችን ተጨማሪ ማብራሪያ ከሚሹ ሀሳቦች መካከል አንስተዋል።

በመጨረሻም የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ ለተነሱ ጉዳዮች የማጠቃለያ ምላሽና አስተያየት የሰጡ ሲሆን

በቀጣይ ባለስልጣኑ የተሻለ የግንኙነት መረብ እንዲፈጠር በማድረግ ለክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ልዩ ልዩ የአቅም ግንባታ ስራዎችና ሥልጠናዎች ላይ በማተኮር የአፈጻጸም ልዩነቶችን የማቀራረብ ተግባር ላይ አበክሮ እንደሚሠራ የገለጹ ሲሆን የምትሠሩባቸው ዘርፎች ከልማት እንቅስቃሴዎች ጋር በቀጥታ የተያያዙ መሆናቸውን በመገንዘብ የቀረበውን ገለጻ በዉይይት ማዳበራቸው የተሰጣቸውን ተግባርና ኃላፊነት ለመወጣት እንደሚረዳቸው ሙሉ ዕምነታቸውን ገልጸው ለተሻለ ተፈጻሚነት ከዚህም ባለፈ ባለስልጣኑ በየትኛውም ዘዴ የተለመደ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጭምር በመግለጽ ለዐዋጅ ማሻሻያው የተዘጋጀውን መርሃ -ግብር አጠናቅቀዋል።

በe-GP ሲስተም ትግበራ ዙሪያ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡

(ግንቦት18/2017 ዓ/ም) የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የe-GP ሲስተምን በሁሉም የፌደራል ተቋማት እና ቅርንጫፎቻቸው እንዲተገበር ማድረጉን ተከትሎ አዋጭነቱን በጥናት ጭምር በማረጋገጥ ወደ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ለማስፋት አቅዶ ግንዛቤ በመፍጠር ለተግባራዊነቱም እየተጋ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡

ይህን ጥረት ተከትሎ ተግባራዊ ካደረጉት መካከል አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቅቆ በባለስልጣኑ በተሰጠው ስልጠና እና ድጋፍ መነሻነት ተግባራዊ እያደረገ ለሌሎች ጭምር አርዓያ እየሆነም ይገኛል፡፡ ለዚህም በማሳያነት የተጠቀሰው የአዲስ አበባ ፋይናስ ቢሮ ግንባር ቀደም ሆኖ ተመርጧል፡፡

ቢሮው የተገበረበትን መንገድ በተሞክሮነት ለማጋራት በዛሬው ዕለት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የመጣውን ልዑክ ተቀብሎ ልምዱን አካፍሏል፡፡ በሂደቱም ስልጠናና ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የስራ ኃላፍዎችና የሲስተም ባለሞያዎች በጋራ በቢሮው ተገኝተዋል፡፡

ልዑኩን ተቀብለው ያነጋገሩት የአዲስ አበባ ፋይናስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ሲስተሙን ለመተግበር የሄዱበትን ሂደት አንድ በአንድ አብራርተው በሂደቱ ውስጥ ባለስልጣኑ የነበረው ሚና ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ ገልጸዋል፡፡

በመቀጠልም ቀደም ሲል ቢሮው ተግባራዊ ሲያደርገው የነበረውን የማንዋል የግዥ ስርዓት ለማዘመን የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓትን ለመተግበር አማራጭ ማድረጉን አስታውሰው ያለውን የአፈጻጸም ልዩነት ለልዑካን ቡድኑ ገልጸዋል፡፡ የቢሮ ኃላፊው አክለውም አሁን ላይ የኤሌክትሮኒክ ግዥ ትግበራ የሚገኙበትን ደረጃ እና የሄዱበትን የአሰራር ሂደት በማሳያነት አንስተው አብራርተዋል፡፡

በመቀጠልም ተሞክሮውን ለመውሰድ በቢሮ የተገኘው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ልዑክ በበኩሉ በአፈጻጸም ሂደቱ ግልጽነት ይሻሉ በሚሏቸው ጉዳዩች ዙሪያ ጥያቄዎችን ያነሱ እና ሀሳብ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄዎች የቢሮው ኃላፊውና የባለስልጣኑ የስራ ኃላፊዎች ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡

አያይዘውም በነበሩበት የትኛውም ሂደት የቢሮው የአፈጻጸም ሂደት እንዲሳለጥ ባለስልጣኑ ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን በድጋሚ ችረዋል፡፡
ቢሮዉ ለeGP ሲስተም ትግበራ ያዘጋጀውን ሠርቨር እና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎች ልዑኩ እንዲጎኘዉ በማድረግ መረሃ-ግብሩ ተጠናቋል፡፡

Business Outreach conference was held on World Bank Financed Investment Projects- procurement.

(May 23/2025) The conference was prepared at Capital Hotel having an agenda of organizing important business outreach to support bidders to know how the World Bank support sectors globally. Participants (supplier side, consultancies, World Bank teams and others) from different sectors were invited.

The opening remark was held by the Director General of the Authority Honorable Mrs. Meseret Meskele, gave special thank for the WB that makes such conference which helps to attract the bidders.

Following this having such commitment and the style of transformational leadership regardless of the Ethiopian Government helps to build not only the national but also the international image building capacity which attract foreign investment that makes us to give more emphasis for sustainable economic development from which the area of procurement is the one that takes more focus to have such success.

She also stated that, the government has designed revised public procurement proclamation No.1333/2024 to modify the governance system as if public procurement provides governments with a powerful tool to achieve their objectives specially in driving business performance efficiency and comparative advantage.

The Director General also forwarded that to have positive effect on procurement practicing Electronic Government System (e-GP) is mandatory to optimize electronic communication.

In conclusion, she stated that digitalization in procurement practice is a strategic importance that embrace the expected transformation to create interconnected world.

Following this brief presentation was delivered by the Bank teams Mr. Arun Kumar (Senior Procurement Specialist in Ethiopia and Sudan and south Sudan, WB). In his presentation Core procurement principles, process of new procurement, frame work and the reasons why the bank has made the change and the market engagement were included.

He also stated about the environmental and social frame work following with relationship among parties, the WB Procurement framework, the common problems with proposals and those solutions that helps to avoid misfortune/bad luck.

Following the presentation, Mr. Ewunetu Abera, CEO at Perago systems, also delivered presentation about the overview of e-GP implementation including end-to-end procurement operations, challenges encountered, mitigation measures to be taken and the new initiatives were also included.

To this end, questions and comprehensive comments were raised by the participants and responses were given by the assigned respondents. Indeed, conclusion remark was also forwarded.

ከሁሉም የፌደራል ባለበጀት መ/ቤቶች የግዥና ንብረት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በግዥ አፈጻጸም ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ የግብዓት ማሰባሠቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 1333/2016 የጸደቀውን አዲሡን አዋጅ ማስፈጸም የሚያስችሉ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያወችን እያዘጋጀ የቆየና ቀደም ሲል የራሱን ሠራተኞች ጨምሮ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት እያወያየ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የተለያዩ ግብዓቶችን በማሠባሰብ ገንቢ አሥተያየቶችን እየጨመረ ማሻሻያዎችን በማከል አጎልብቶ ተጨማሪ አስቻይና አሠሪ ግብዓቶችን ለመሠብሠብ ስራውን በዋናነት ተግባራዊ ከሚያደርጉት የሁሉም የፌደራል ተቋማት የግዥና ንብረት የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ለመቀበል የተዘጋጀ መድረክ ነው።

READ MORE