Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

General

ከሁሉም ባንኮችና ኢንሹራንሶች ጋር በኢጂፒ ሲሰተም ትስስር ትግበራ ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በመክፈቻ ንግግራቸዉ ባለስልጣኑ የዲጅታላይዜሽን እና የትራንስፎርሜሽን ጉዞን ከተቀላቀለ ጊዜ ጀምሮ አሰራርን ዘመናዊ፤ቀልጣፋና ዉጤታማ ለማድረግ በዘርፉ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ተቋም መሆኑን አስታዉሰዉ በተለይም የኢጂፒ ሲስተምን በመጠቀም ቀደም ሲል የተተገበሩና በቀጣይም የተሻሻሉ ትግበራዎችን ጭምር የሲስተሙ አካል በማድረግ ከመተግበር በዘለለ ለንግዱ ማህበረሰብ በኢጂፒ ሲስተም ዙሪያ በቂ መረጃ እንዲኖረዉ በአካል ከሚሰጠዉ ድጋፍ በተጨማሪ በበይነ-መረብ ለመስጠት የሚያሥችል ስርዓት ተጠናቅቆ ወደ ተግባር መገባቱን ጭምር ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡

አያይዘዉም ሲስተሙን ቀደም ሲል ከሌሎች ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ተግባር መከናወኑን ገልጸዉ የዚሁ መድረክ ዋነኛ ዓላማም ባንኮችንና ኢንሹራንሶችን ከመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ጋር ማስተሳሰር መሆኑን በመጠቆም በተለይም ከግዥ ጋር የተያያዙ ማስተግበሪያዎችን ሲስተሙን ተጠቅመዉ የንግዱ ማህበረሰብ (አቅራቢዎች) ደንበኛ ከሆኑበት የትኛዉም የባንክና የኢንሹራንስ አማራጮች በኦንላይን እንዲያዙ የሚስችላቸዉን የሲስተም ዝርጋታ ትዉዉቅ በማድረግ በይፋ ለማስጀመር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

READ MORE >>

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የህብር ቀንን አከበር፡፡


ዻጉሜ 4/2016 የህብር ቀን የሚል ሰያሜ ተሰጥቶት በመላ ሀገሪቱ በተለያየ ሁነት መከበሩን ተከትሎ ነዉ ባለስልጣኑም የህብር ቀንን በአብሮነት ለማሳለፍና ለማክበር የወሰነዉ፡፡

በዓሉን መላዉ የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች በስፍራዉ በመገኘት ያከበሩ ሲሆን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በቦታዉ ተገኝተዉ የእንኳን አደረሳቹህ መልዕክትና የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል፡፡

READ MORE >>