Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

News

ባለስልጣኑ ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ጽ/ቤት ጋር የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረመ፡፡

የመ/ግ/ን/ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በንግግራቸዉ ለኢጂፒ ሲስተም ትስስር ትግበራ አጋዥ የሆነ የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም መድረኩ መዘጋጀቱን የገለጹ ሲሆን ትስስሩ በግዥዉ ዘርፍ ያሉ የአሰራር ጉድለቶችን ለማስወገድና ማነቆዎችን ጭምር ለመፍታት ብሎም ከብክነት በጸዳ መንገድ ለመተግበር ያስችላል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

አያይዘዉም  ሲሰተሙን ከብሄራዊ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰሩ ያለዉን ፋይዳ ሲገልጹ ዕዉነተኛ ማንነትን በማረጋገጥ የሲስተሙን ተዓማኒነት ከፍ ማድረግ ቀዳሚዉ ነዉ ብለዋል፡፡

READ MORE >>

ከሁሉም ባንኮችና ኢንሹራንሶች ጋር በኢጂፒ ሲሰተም ትስስር ትግበራ ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በመክፈቻ ንግግራቸዉ ባለስልጣኑ የዲጅታላይዜሽን እና የትራንስፎርሜሽን ጉዞን ከተቀላቀለ ጊዜ ጀምሮ አሰራርን ዘመናዊ፤ቀልጣፋና ዉጤታማ ለማድረግ በዘርፉ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ተቋም መሆኑን አስታዉሰዉ በተለይም የኢጂፒ ሲስተምን በመጠቀም ቀደም ሲል የተተገበሩና በቀጣይም የተሻሻሉ ትግበራዎችን ጭምር የሲስተሙ አካል በማድረግ ከመተግበር በዘለለ ለንግዱ ማህበረሰብ በኢጂፒ ሲስተም ዙሪያ በቂ መረጃ እንዲኖረዉ በአካል ከሚሰጠዉ ድጋፍ በተጨማሪ በበይነ-መረብ ለመስጠት የሚያሥችል ስርዓት ተጠናቅቆ ወደ ተግባር መገባቱን ጭምር ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡

አያይዘዉም ሲስተሙን ቀደም ሲል ከሌሎች ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ተግባር መከናወኑን ገልጸዉ የዚሁ መድረክ ዋነኛ ዓላማም ባንኮችንና ኢንሹራንሶችን ከመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ጋር ማስተሳሰር መሆኑን በመጠቆም በተለይም ከግዥ ጋር የተያያዙ ማስተግበሪያዎችን ሲስተሙን ተጠቅመዉ የንግዱ ማህበረሰብ (አቅራቢዎች) ደንበኛ ከሆኑበት የትኛዉም የባንክና የኢንሹራንስ አማራጮች በኦንላይን እንዲያዙ የሚስችላቸዉን የሲስተም ዝርጋታ ትዉዉቅ በማድረግ በይፋ ለማስጀመር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

READ MORE >>

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የህብር ቀንን አከበር፡፡


ዻጉሜ 4/2016 የህብር ቀን የሚል ሰያሜ ተሰጥቶት በመላ ሀገሪቱ በተለያየ ሁነት መከበሩን ተከትሎ ነዉ ባለስልጣኑም የህብር ቀንን በአብሮነት ለማሳለፍና ለማክበር የወሰነዉ፡፡

በዓሉን መላዉ የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች በስፍራዉ በመገኘት ያከበሩ ሲሆን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በቦታዉ ተገኝተዉ የእንኳን አደረሳቹህ መልዕክትና የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል፡፡

READ MORE >>

በግዥ አፈጻጸምና ንብርት አስተዳደር ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በሀገራችን ከሁሉም (ከትግራይ ክልል ዉጪ) ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በግዥ አፈጻጸምና ንብርት አስተዳደር ዙሪያ በሚስተዋሉ ተግዳሮቶች፤ በወቅታዊ የገበያ ሁኔታ እና በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ከሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ሐምሌ 23 እና 24 ቀን 2014 ዓ.ም ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሶስተኛ ዙር የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ ግልፅ፣ ዘመናዊ ቀልጣፋና ውጤታማ የመንግስት ግዥ አፈፃፀምና ንብረት አስተዳደር ማስፈን፣ የመንግስትን ንብረት በጥንቃቄ የመያዝ፣ የመጠቀምና የመቆጣጠር እንዲሁም ንብረቱ አገልግሎቱ ሲያበቃ በወቅቱና በተገቢው መንገድ እንዲወገድ ማስቻል  ነው፡፡

READ MORE >>