ከሁሉም የፌደራል ባለበጀት መ/ቤቶች የግዥና ንብረት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በግዥ አፈጻጸም ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ የግብዓት ማሰባሠቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 1333/2016 የጸደቀውን አዲሡን አዋጅ ማስፈጸም የሚያስችሉ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያወችን እያዘጋጀ የቆየና ቀደም ሲል የራሱን ሠራተኞች ጨምሮ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት እያወያየ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የተለያዩ ግብዓቶችን በማሠባሰብ ገንቢ አሥተያየቶችን እየጨመረ ማሻሻያዎችን በማከል አጎልብቶ ተጨማሪ አስቻይና አሠሪ ግብዓቶችን ለመሠብሠብ ስራውን በዋናነት ተግባራዊ ከሚያደርጉት የሁሉም የፌደራል ተቋማት የግዥና ንብረት የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ለመቀበል የተዘጋጀ መድረክ ነው።
READ MORE