Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

News

ከሁሉም የፌደራል ባለበጀት መ/ቤቶች የግዥና ንብረት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በግዥ አፈጻጸም ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ የግብዓት ማሰባሠቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 1333/2016 የጸደቀውን አዲሡን አዋጅ ማስፈጸም የሚያስችሉ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያወችን እያዘጋጀ የቆየና ቀደም ሲል የራሱን ሠራተኞች ጨምሮ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት እያወያየ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የተለያዩ ግብዓቶችን በማሠባሰብ ገንቢ አሥተያየቶችን እየጨመረ ማሻሻያዎችን በማከል አጎልብቶ ተጨማሪ አስቻይና አሠሪ ግብዓቶችን ለመሠብሠብ ስራውን በዋናነት ተግባራዊ ከሚያደርጉት የሁሉም የፌደራል ተቋማት የግዥና ንብረት የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ለመቀበል የተዘጋጀ መድረክ ነው።

READ MORE

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች የሰንደቅ ዓላማ ቀንን አከበሩ፡፡

የባለስልጣኑ አመራሮችና ሠራተኞች 17ኛዉን የሰንደቅ ዓላማ ቀን ያከበሩት ከፕላንና ልማት ሚኒሰቴርና ከመንግስት ግዥ አገልግሎት አመራርና ሰራተኞች ጋር በጋራ በመሆን ነዉ፡፡

”ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ሃሳብ ነዉ ያከበሩት፡፡

READ MORE >>

ባለስልጣኑ ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ጽ/ቤት ጋር የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረመ፡፡

የመ/ግ/ን/ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በንግግራቸዉ ለኢጂፒ ሲስተም ትስስር ትግበራ አጋዥ የሆነ የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም መድረኩ መዘጋጀቱን የገለጹ ሲሆን ትስስሩ በግዥዉ ዘርፍ ያሉ የአሰራር ጉድለቶችን ለማስወገድና ማነቆዎችን ጭምር ለመፍታት ብሎም ከብክነት በጸዳ መንገድ ለመተግበር ያስችላል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

አያይዘዉም  ሲሰተሙን ከብሄራዊ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰሩ ያለዉን ፋይዳ ሲገልጹ ዕዉነተኛ ማንነትን በማረጋገጥ የሲስተሙን ተዓማኒነት ከፍ ማድረግ ቀዳሚዉ ነዉ ብለዋል፡፡

READ MORE >>

ከሁሉም ባንኮችና ኢንሹራንሶች ጋር በኢጂፒ ሲሰተም ትስስር ትግበራ ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በመክፈቻ ንግግራቸዉ ባለስልጣኑ የዲጅታላይዜሽን እና የትራንስፎርሜሽን ጉዞን ከተቀላቀለ ጊዜ ጀምሮ አሰራርን ዘመናዊ፤ቀልጣፋና ዉጤታማ ለማድረግ በዘርፉ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ተቋም መሆኑን አስታዉሰዉ በተለይም የኢጂፒ ሲስተምን በመጠቀም ቀደም ሲል የተተገበሩና በቀጣይም የተሻሻሉ ትግበራዎችን ጭምር የሲስተሙ አካል በማድረግ ከመተግበር በዘለለ ለንግዱ ማህበረሰብ በኢጂፒ ሲስተም ዙሪያ በቂ መረጃ እንዲኖረዉ በአካል ከሚሰጠዉ ድጋፍ በተጨማሪ በበይነ-መረብ ለመስጠት የሚያሥችል ስርዓት ተጠናቅቆ ወደ ተግባር መገባቱን ጭምር ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡

አያይዘዉም ሲስተሙን ቀደም ሲል ከሌሎች ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ተግባር መከናወኑን ገልጸዉ የዚሁ መድረክ ዋነኛ ዓላማም ባንኮችንና ኢንሹራንሶችን ከመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ጋር ማስተሳሰር መሆኑን በመጠቆም በተለይም ከግዥ ጋር የተያያዙ ማስተግበሪያዎችን ሲስተሙን ተጠቅመዉ የንግዱ ማህበረሰብ (አቅራቢዎች) ደንበኛ ከሆኑበት የትኛዉም የባንክና የኢንሹራንስ አማራጮች በኦንላይን እንዲያዙ የሚስችላቸዉን የሲስተም ዝርጋታ ትዉዉቅ በማድረግ በይፋ ለማስጀመር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

READ MORE >>