Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

News

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የህብር ቀንን አከበር፡፡


ዻጉሜ 4/2016 የህብር ቀን የሚል ሰያሜ ተሰጥቶት በመላ ሀገሪቱ በተለያየ ሁነት መከበሩን ተከትሎ ነዉ ባለስልጣኑም የህብር ቀንን በአብሮነት ለማሳለፍና ለማክበር የወሰነዉ፡፡

በዓሉን መላዉ የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች በስፍራዉ በመገኘት ያከበሩ ሲሆን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በቦታዉ ተገኝተዉ የእንኳን አደረሳቹህ መልዕክትና የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል፡፡

READ MORE >>

በግዥ አፈጻጸምና ንብርት አስተዳደር ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በሀገራችን ከሁሉም (ከትግራይ ክልል ዉጪ) ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በግዥ አፈጻጸምና ንብርት አስተዳደር ዙሪያ በሚስተዋሉ ተግዳሮቶች፤ በወቅታዊ የገበያ ሁኔታ እና በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ከሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ሐምሌ 23 እና 24 ቀን 2014 ዓ.ም ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሶስተኛ ዙር የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ ግልፅ፣ ዘመናዊ ቀልጣፋና ውጤታማ የመንግስት ግዥ አፈፃፀምና ንብረት አስተዳደር ማስፈን፣ የመንግስትን ንብረት በጥንቃቄ የመያዝ፣ የመጠቀምና የመቆጣጠር እንዲሁም ንብረቱ አገልግሎቱ ሲያበቃ በወቅቱና በተገቢው መንገድ እንዲወገድ ማስቻል  ነው፡፡

READ MORE >>

ከዓለም ባንክ የተዉጣጣ ልዑክ የኤሌክትሮኒክ ግዥ አፈጻጸምን ገመገመ፡፡

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከክልል አቻ የግዥና ንብረት ተቆጣጣሪ ተቋም እንዲሁም የማዕከል ግዥ ፈፃሚ አካላት ጋር በባህርዳር ከተማ የምክክር መድረክ እያከናወነ ይገኛል፡፡
የምክክር መድረኩ ከሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከሁሉም ክልሎች (ከትግራይ ክልል በስተቀር) የተውጣጡ የግዥ ተቆጣጣሪነት ሚና ያላቸው ተቋማት እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

READ MORE

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በስትራይድ ኢትዮጵያ ኤክስፖ 2024 ማጠቃለያ ፕሮግራም የእዉቅና ሽልማት ተበረከተለት፡፡

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር አዘጋጅነት በሳይንስ ሙዚየም በተካሄደዉ ስትራይድ አዋርድ 2024 ኤክስፖ ብቃት የመለያ ምልክታቸው፤ የአመራር ጥበብ ግለ-ተሰጥኦቸው የሆኑት የዚሁ ቀናዒ ተግባር መሪ(ባለቤት) የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሃጂ ኢብሳ በስፍራው በመገኘት ሽልማታቸውን በክብር ተቀብለዋል፡፡

ባለስልጣኑ በኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ትግበራ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያበረከተዉ አስተዋጽኦ ከፍ ባለና በላቀ ዉጤት ታጅቦ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ የሃገር ሀብት በተገቢው የግብይት ስርዓት እንዲፈጸም በማድረግ ከብክነት በመታደጉ ረገድ ለነበረው አበርክቶ እና ጉልህ ተሳትፎ የተሰጠ እውቅና መሆኑ ተገልጿል፡፡

READ MORE