Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

General

በፌዴራል መንግስት የተያዙ የልማት ድርጅቶች የግዥ መመሪያ 1070/2017 ላይ ስልጠና እና የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

(ነሐሴ 26/2017 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በፌዴራል መንግስት ከተያዙ የልማት ድርጅቶች ጋር የግዥ አፈጻጸም እና የንብረት አያያዝን በሚመለከት ውይይት እያደረገ ይገኛል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአሰራር ስርዓቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ ቀልጣፋ፣ ታዓማኒ፣ አካታች እና ጥራት ያለው ለማድረግ ከፍተኛ ስራ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን የግዥ አዋጁን ከማሻሻል ጀምሮ የፌዴራል ግዥ መመሪያን፣ የፌዴራል ንብረት መመሪያን፣ በፌዴራል መንግስት ባለቤትነት የተያዙ የልማት ድርጅቶች ግዥ መመሪያን እና የመድሐኒትና የህክምና ቁሳቁሶች መመሪያን በማውጣት ስራ ላይ እንዲውሉ አድርጓል።

በአዋጅ 1333/2016 ከተካተቱ አበይት ተግባራት አንዱ በፌዴራል መንግስት የተያዙ የልማት ድርጅቶች ግዛቸውን በኤሌክትሮኒክ ስርዓት እንዲፈጽሙ የሚያስችል ሲሆን የግዥ መመሪያውም የስራ ባህሪያቸውን መሰረት ያደረግ እንዲሆን የማድረግ ስራ ተሰርቷል።

ይህን ተከትሎም የልማት ድርጅቶች ውጤታማ የግዥና ንብረት አስተዳደር ስርዓት ሊገነቡ በሚችሉበት እና መመሪያውን ውጤታማ በሆነ መንገድ ሊፈጽሙ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።

የውይይት መነሻ ጽሁፍ እና በ2017 በጀት ዓመት የተተገበሩ አበይት ክንውኖችን ለውይይት ያቀረቡት የግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ውጤታማ የግዥ እቅድ ለውጤታማ ስራ ክንውን መሰረት መሆኑን ያብራሩ ሲሆን ግዥ ያለ እቅድ መፈጸም እንደሌልበትም አብራርተዋል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት የመንግስት የኤሌክትሮኒክ ግዥ አካታችነትን በማስፈን፣ ግልጽ የአሰራር ስርዓትን በመፈጠር፣ የተሳታፊን ቁጥር በመጨመር፣ ቀልጣፋ እና ጥራት ያለው የግዥ ሂደትን እውን በማድረግ በኩል ችግር ፈቺ ስርዓት መሆኑን አመላክተዋል።

የክብርት ወ/ሮ መሰረትን ገለጻ ተከትሎ በፌዴራል መንግስት ባለቤትነት የተያዙ የልማት ድርጅቶች የግዥ መመሪያ 1070/2017 ላይ በአቶ ገብያው ይታይህ እና በወ/ሮ አየናቸው ቸርነት ስልጠና እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን ስልጠናውም ለሁለት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።

በአገልግሎት አስተዳደር ሪፎርም የተግባር ምዕራፍ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ።

(ነሐሴ 25/2017 ዓ/ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት የለውጥ ዝግጅት ምዕራፍን በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን ተከትሎ በአገልግሎትና አስተዳደር የተግባር ምዕራፍ ዕቅድ ዙሪያ ከአምራሩና ከሰራተኞች ጋር ውይይት አድርጓል።

ውይይቱ ተቋማዊ ባህልን መገንባት እና የትግበራ ምዕራፉን በተሳካ ሁኔታን ለመወጣት ያለመ ሲሆን ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ በተነሳሽነት እና በአንድ ዓላማ ወደ ትግበራ መግባት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

በውይይቱ በአገልግሎትና በአስተዳደር ሪፎርም የተሰሩ አበይት ስራዎችና በትግበራ ምዕራፉ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራት በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት ቀርቦ ውይይት ተደርጐበታል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት በገለጻቸው በሪፎርም ስራው የአመራሩ እና የሰራተኛው ተነሳሽነት፣ ተግባራትን ለመፈጸም የነበረ ቅንነት፣ ቁርጠኝነትና ተግባቦት እጅግ የሚያስመሰግን የነበረ ሲሆን ውጤቱም የሁሉም አመራርና ሰራተኛ ልፋት፣ ጥረትና ድካም ውጤት ነው በማለት ገልፀዋል።

አያይዘውም በሪፎርም የእቅድ ምዕራፉ ላይ ከ21 መመሪያዎች እና የአሰራር ስርዓቶች መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል። በተለይም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ስራዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ስራ መሰራቱ የተገለጸ ሲሆን በዚህም ኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ (e-GP) ላይ ከ29,340 አቅራቢዎች መመዝገባቸው፣ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ግዣቸውን በኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) መፈፀም መቻላቸው እንዲሁም በተሽከርካሪ ስምሪትና ቁጥጥር ስርዓት (e- Fleet Management)፣ ቅሬታ እና ጥቆማ መቀበያን ዲጂታላይ በማድረግ፣ በኤሌክትሮኒክ ትምህርት (e-Learning)፣ ዲጂታል ደብዳቤ (e- Lettering) ስርዓቶች ውጤታማ ሆነው እየተተገበሩ መሆናቸው ተጠቅሷ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀጣይ የትግበራ ምዕራፍ ላይ አስተዳደርና አደረጃጀት፣ ዘመናዊ የሰራተኞች መረጃ አያያዝ፣ ፍትሐዊና ተደራሽ የመንግስት ግዥ፣ ዲጂታል የመንግስት ግዥ፣ ብዝሃነትና አካታችነት፣ የሰራተኞች ብቃትና ምዘና ማረጋገጥ በሚቻልበተ ሁኒታ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተብራርቷል።

የክብርት ዋና ዳይሬክትሯን ገለጻ ተከትሎ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በዋና ዳይሬክተሯ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

በመጨረሻም በ2017 በጀት ዓመት ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ አመራሮች፣ ስራ ክፍሎች እና ሰራተኞች የእውቅና እና የምስጋና የምስክረ ወረቀት በማበርከት የዕለቱ መርሃግብር ተጠናቋል።

Consultation meeting was held on the status of e-GP implementation.

The World bank (WB) team including Dr.Rajish (senior procurement specialist at WB) has come to consult the way how the system is practical, to heard the enhancement briefing, to evaluate the current performance of the system and its outcome and even what benefit that we gain, our country Ethiopia has gain from such practice, what challenges face while practicing it and to give constructive comments that helps to revise the planned activities.

The opening remark was delivered by the Director General of the Public procurement Authority Honourable Mrs. Meseret Meskele, she gave special thank for the WB team that gives such opportunity which helps the authority to enhance system implementation.

The Director General also forwarded that to have positive effect on practicing Electronic Government System (e-GP) is mandatory to optimize electronic communication that is why the government has designed revised public procurement proclamation No.1333/2024 and fully aligned with e-GP system having its own new directives which has been approved.

She also justified about the benefits what we have gain as a country, like the reduction of paper consumption, transportation cost, promoting transparency, and other related instances in her speech.

Following this, Briefing was also held by the Vice Project Manager Mr. Yafet Mekonen, starting from the general overview of what will be in his presentation, following with the legal and conceptual framework of the system, the overall status and system integration activities in relation with upgrading the system, the challenges, mitigation solution and the way forward were included.

Chance was also given for the developer to deliver presentation about e-GP enhancement on their side, Mr, Ewunetu Abera( the developer of the e-GP system) give briefing about all the modules, challenges and possible solutions what they plan to sustain the system.                                                                                                                                                                                                              

Following with the aforementioned presentation, the WB team had also raised the issue related to the system related comments and questions) and international consultancy, cooperation to own (take over) the system from the developer, experience sharing from other countries and addressing the issue of problems and sustainability of the system.

Suggestions and responses were given by the Director General of FPPA, the Vice Manager and others. Indeed, conclusion remarks were also forwarded.

ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

(ነሐሴ 11/2017 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ለአመራርና ለሰራተኞች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና አጠናቋል። ስልጠናው በፌዴራል መንግስት የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 1073/2017 እና በፌዴራል መንግስት የንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1095/2017 ያተኮረ ሲሆን ዋና ዓላማውም አመራርና ሠራተኞች መመሪያዎችን አውቀው አገልግሎት መስጠት እንዲችሉና በመመሪያዎች ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖሯቸው ብሎም  ችግሮችን የመፍታት አቅም እንዲዳብሩ ለማስቻል ነው።

በፌዴራል መንግስት የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 1073/2017 ላይ ስልጠና የሰጡት በኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የመንግስት ግዥና ንብረት ማሻሻያና አቅም  ግንባታ ዴስክ ኃላፊ አቶ ናትናኤል አስፋው ሲሆኑ አዲሱ መመሪያ ቀድሞ ከነበረው መመሪያ በብዙ መንገዶች የተለዬ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ አቶ ናትናኤል በገለጻቸው የግዥ መርሆች ከ5 ወደ 7 ከፍ የተደረጉ መሆናቸውን እነዚህም የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ጥቅም ማስገኘት፣ በተወዳዳሪዎችና ተጫራቾች መካከል አድሎዎ አለማድረግ፣ ግልጽነትና ፍትሐዊነት፣ ግዥው በአካባቢ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የማያስከትል እንዲሁም የህይወት ዘመን ወጪን ትንተናን ከግምት ያስገባ እና መልሶ መጠቀምን የሚያበረታታ፣ ቀልጣፋ፣ ውጤታማ እና ወጪ ቆጣቢ የሆነ፣ የግዥ አፈጻጸም ተግባራትን በታማኝነት መፈጸም፣ በግዥ አፈጻጸም ሂደት የሚሰጡ ውሳኔዎችና የሚወሰዱ እርምጃዎች ተጠያቂነት የሚያስከትሉ መሆናቸው፣ የቴክኖሎጂ ፈጠራን ማበረታት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አቶ ናትናኤል አያይዘውም አዲሱ መመሪያ የስራ ፈጠራን የሚያበረታታና አዳዲስ የግዥ ስልቶች የተካተቱበት እንዲሁም የተጋነነና የተሰበረ ዋጋ በመቶኛ የመወሰነ መሆኑን ያብራሩ ሲሆን መመሪያውን ማንበብ፣ ማወቅና ማሳወቅ የተቋሙ አመራርና ሰራትገኛ ሀላፊነት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡:

በፌዴራል መንግስት የንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1095/2017 ላይ ስልጠና የሰጡት በኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የግዥና ንብረት እቅድና መረጃ ዴስክ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዘበነ ገዛኸ በበኩላቸው አዲሱ የንብረት አስተዳደር መመሪያ ተለምዷዊ አሰራርን በማስቀረትና ዲጂታል አሰራርን በማስፈን በኩል ትልቅ ለውጥ ያመጣ ነው ያሉ ሲሆን ንብረትን በእቅድ መምራት፣ ንብረትን በአግባቡ ይዞ ለሚፈለገው አገልግሎት እንዲውል ማድረግ፣ የንብረት አወጋገድን በአግባቡ ማከናወን እና በግንባታ ላይ ያሉ ንብረቶች የንብረት ስራ ክፍል ክትትል ማድረግ እንዲሚጠበቅበት መመሪያው እንደሚያስገነዝብ አብራርተዋል፡፡

ከስልጠናው በኋላ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለተጠየቁት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያን ተሰጥቶ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡