Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

Author: Yonas Habesha

ደሜን ለወገኔ የደም ልገሳ መርሃግብር ተከናወነ፡፡

(ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራትኞች በክረምት ወራት ከዋናው ስራቸው ጎን ለጎን የተለያዩ የብጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዚህም በእንጦጦ እና በላፍቶ ለሶስት ጊዜያት የችግኝ ተከላ መርሃግብር ያከናወኑ ሲሆን በዛሬው እለትም “ደም በመለገስ ህይወትን እንታደግ” በሚል መሪ ቃል የደም በመለገስ መርህግብር አከናውነዋል፡፡

በቀሪ የክረምት ወራትም የችግኝ ተከላ፣ የምገባ፣ አቅመ ደካሞችን የማገዝና ሌሎች የበጎ አድራጎት ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ ሲሆን ይህ የደም ልገሳ መርሃግብርም የክረምቱ የበጎ አድራጎት አንዱ አካል ነው።

“በመትከል ማንሰራራት” የችግኝ ተከላ መርሃግብር እንደቀጠለ ነው፡፡

(ሀምሌ 16/2017 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች  3ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃግብር በእንጦጦ ፓርክ በተዘጋጀላቸው ስፍራ አከናውነዋል።

የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌን ጨምሮ ሁሉም አምራርና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን በእለቱ ከ2000 በላይ ችግኞችን መትከል ተችሏል፡፡ ይህም እንደሀገር የተያዘውን “በመትከል ማንሰራራት” አንዱ አካል ሲሆን በቀሪ የክረምት ጊዜም የችግኝ ተከላው መርሃግብር የሚቀጥል ይሆናል፡፡

ኢትዮጵያ ከአለፉት አመታት ጀምሮ የአየር ንብረት ለውጥን ለመግታት አረንጓዴ አሻራ መርሃግብርን (Green Legacy Initiative) ቀርጻ እየተንቀሳሰች የሚገኝ ሲሆን በዚህ የክረምት ወቅትም 7.5 ቢሊዮን ችግኞችን እንደሚተከሉ ይጠበቃል፡፡