Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

(ነሐሴ 11/2017 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ለአመራርና ለሰራተኞች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና አጠናቋል። ስልጠናው በፌዴራል መንግስት የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 1073/2017 እና በፌዴራል መንግስት የንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1095/2017 ያተኮረ ሲሆን ዋና ዓላማውም አመራርና ሠራተኞች መመሪያዎችን አውቀው አገልግሎት መስጠት እንዲችሉና በመመሪያዎች ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖሯቸው ብሎም  ችግሮችን የመፍታት አቅም እንዲዳብሩ ለማስቻል ነው።

በፌዴራል መንግስት የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 1073/2017 ላይ ስልጠና የሰጡት በኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የመንግስት ግዥና ንብረት ማሻሻያና አቅም  ግንባታ ዴስክ ኃላፊ አቶ ናትናኤል አስፋው ሲሆኑ አዲሱ መመሪያ ቀድሞ ከነበረው መመሪያ በብዙ መንገዶች የተለዬ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ አቶ ናትናኤል በገለጻቸው የግዥ መርሆች ከ5 ወደ 7 ከፍ የተደረጉ መሆናቸውን እነዚህም የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ጥቅም ማስገኘት፣ በተወዳዳሪዎችና ተጫራቾች መካከል አድሎዎ አለማድረግ፣ ግልጽነትና ፍትሐዊነት፣ ግዥው በአካባቢ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የማያስከትል እንዲሁም የህይወት ዘመን ወጪን ትንተናን ከግምት ያስገባ እና መልሶ መጠቀምን የሚያበረታታ፣ ቀልጣፋ፣ ውጤታማ እና ወጪ ቆጣቢ የሆነ፣ የግዥ አፈጻጸም ተግባራትን በታማኝነት መፈጸም፣ በግዥ አፈጻጸም ሂደት የሚሰጡ ውሳኔዎችና የሚወሰዱ እርምጃዎች ተጠያቂነት የሚያስከትሉ መሆናቸው፣ የቴክኖሎጂ ፈጠራን ማበረታት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አቶ ናትናኤል አያይዘውም አዲሱ መመሪያ የስራ ፈጠራን የሚያበረታታና አዳዲስ የግዥ ስልቶች የተካተቱበት እንዲሁም የተጋነነና የተሰበረ ዋጋ በመቶኛ የመወሰነ መሆኑን ያብራሩ ሲሆን መመሪያውን ማንበብ፣ ማወቅና ማሳወቅ የተቋሙ አመራርና ሰራትገኛ ሀላፊነት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡:

በፌዴራል መንግስት የንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1095/2017 ላይ ስልጠና የሰጡት በኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የግዥና ንብረት እቅድና መረጃ ዴስክ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዘበነ ገዛኸ በበኩላቸው አዲሱ የንብረት አስተዳደር መመሪያ ተለምዷዊ አሰራርን በማስቀረትና ዲጂታል አሰራርን በማስፈን በኩል ትልቅ ለውጥ ያመጣ ነው ያሉ ሲሆን ንብረትን በእቅድ መምራት፣ ንብረትን በአግባቡ ይዞ ለሚፈለገው አገልግሎት እንዲውል ማድረግ፣ የንብረት አወጋገድን በአግባቡ ማከናወን እና በግንባታ ላይ ያሉ ንብረቶች የንብረት ስራ ክፍል ክትትል ማድረግ እንዲሚጠበቅበት መመሪያው እንደሚያስገነዝብ አብራርተዋል፡፡

ከስልጠናው በኋላ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለተጠየቁት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያን ተሰጥቶ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *