መፍትሔ ሰጪ መሪ ለመሆን የተቋሙን አሰራር እና የአሰራር ስርዓቶች ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ
(ነሐሴ 09/2017 ዓ/ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዘመናዊ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ስርዓት በማጠናከር በ2022 ዓ/ም በአፍሪካ አርዓያ ከሆኑ ተቋማት አንዱ የመሆን ርዕይን ሰንቆ በትጋት እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡ በዚህም አዋጁን ማሻሻል ጨምሮ ከ20 በላይ መመሪያዎችን ተግባራዊ አድርጓል፡፡
በዚህም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አመራሩና ሰራተኞች መመሪያዎችን አውቀው እንዲተገብሩ ለማስቻል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡ በስልጠናው ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳየሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት እንደገለጹት መፍትሔ ሰጪ እና አገልጋይ መሪ ለመሆን የተቋሙን አሰራር እና የአሰራር ስርዓቶች ማወቅ አስፈላጊ ነው፡፡ ስለሆነም የግዥ አፈጻጸምና የንብረት አስተዳደር መመሪያዎችን አውቆ ለመተግበር ስልጠና መስጠቱ አስፈልጓል ብለዋል፡፡
የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ስልጠና እየሰጡ የሚገኙት አቶ ናትናኤል አስፋው በበኩላቸው በተቋሙ ውስጥ ውጤታማ ስራ ለማከናወን የተቋሙን የጋራ እሴት የሆነውን ርዕይ ማወቅና ስራዎችን ከተቋሙ ርዕይ አንጻር መፈጸም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በስልጠናው ስራ አስፈጻሚዎች፣ ዴስክ ሀላፊዎች፣ ቡድን መሪዎች እና ከፍተኛ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው እስከ ነሐሴ 11/2017 ዓ/ም የሚቀጥል ይሆናል፡፡






0 Comments