ደሜን ለወገኔ የደም ልገሳ መርሃግብር ተከናወነ፡፡
(ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራትኞች በክረምት ወራት ከዋናው ስራቸው ጎን ለጎን የተለያዩ የብጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዚህም በእንጦጦ እና በላፍቶ ለሶስት ጊዜያት የችግኝ ተከላ መርሃግብር ያከናወኑ ሲሆን በዛሬው እለትም “ደም በመለገስ ህይወትን እንታደግ” በሚል መሪ ቃል የደም በመለገስ መርህግብር አከናውነዋል፡፡
በቀሪ የክረምት ወራትም የችግኝ ተከላ፣ የምገባ፣ አቅመ ደካሞችን የማገዝና ሌሎች የበጎ አድራጎት ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ ሲሆን ይህ የደም ልገሳ መርሃግብርም የክረምቱ የበጎ አድራጎት አንዱ አካል ነው።













0 Comments