Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

የእውቅና እና የምስጋና መርሃግብር ተካሄደ።

(ነሐሴ 05/2017 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአሰራር ስርዓቱን አዘምኖ፣ ግልፅ፣ ቀልጣፋ እና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ አዋጁን ማሻሻል ዋነኛው የለውጥ መነሻ ሲሆን አዋጁን ተከትሎምም መመሪያዎችና ማስፈፀሚያ ማኑዋሎች ተዘጋጅተው ወደ ትግበራ ተግብቷል።

በዚህም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በመመሪያ ዝግጁቱ ላይ ለተሳተፉና ለለውጡ ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ለነበራቸው ተቋማት፣ አመራርና ባለሙያዎች እውቅና ሰጥቷል።

በእውቅና እና በምስጋና መርሃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ፈቃዱ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም መሰል መመሪያዎች የሚዘጋጁት በአማካሪ በመሆኑ ብዙ ገንዘብ ያስወጣ የነበረ ሲሆን አዋጁን ተከትሎ የወጡ መመሪያዎች በውስጥ አቅም ብሎም አሳታፊ በሆነ መልኩ ስለተዘጋጁ ወጪን ማዳን መቻሉ እንደተጠበቀ ሆኖ የመመሪያዎች ጥራትም ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው የመመሪያ ዝግጅት ስራው እጅግ አድካሚ የነበረ ቢሆንም  ሳትሳሱ ያለምንም ክፍያ እውቀታችሁን፣ ጊዜያችሁን እና ጉልበታችሁን  ለተቋማችን ስለሰጣችሁ ምስጋና ይገባችኋል፤ ወደፊትም አብረን ሆነን ብዙ ለውጦችን እናመጣለን ብለዋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *