Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

በአገልግሎት አስተዳደር ሪፎርም የተግባር ምዕራፍ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ።

(ነሐሴ 25/2017 ዓ/ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት የለውጥ ዝግጅት ምዕራፍን በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን ተከትሎ በአገልግሎትና አስተዳደር የተግባር ምዕራፍ ዕቅድ ዙሪያ ከአምራሩና ከሰራተኞች ጋር ውይይት አድርጓል።

ውይይቱ ተቋማዊ ባህልን መገንባት እና የትግበራ ምዕራፉን በተሳካ ሁኔታን ለመወጣት ያለመ ሲሆን ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ በተነሳሽነት እና በአንድ ዓላማ ወደ ትግበራ መግባት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

በውይይቱ በአገልግሎትና በአስተዳደር ሪፎርም የተሰሩ አበይት ስራዎችና በትግበራ ምዕራፉ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራት በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት ቀርቦ ውይይት ተደርጐበታል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት በገለጻቸው በሪፎርም ስራው የአመራሩ እና የሰራተኛው ተነሳሽነት፣ ተግባራትን ለመፈጸም የነበረ ቅንነት፣ ቁርጠኝነትና ተግባቦት እጅግ የሚያስመሰግን የነበረ ሲሆን ውጤቱም የሁሉም አመራርና ሰራተኛ ልፋት፣ ጥረትና ድካም ውጤት ነው በማለት ገልፀዋል።

አያይዘውም በሪፎርም የእቅድ ምዕራፉ ላይ ከ21 መመሪያዎች እና የአሰራር ስርዓቶች መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል። በተለይም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ስራዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ስራ መሰራቱ የተገለጸ ሲሆን በዚህም ኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ (e-GP) ላይ ከ29,340 አቅራቢዎች መመዝገባቸው፣ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ግዣቸውን በኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) መፈፀም መቻላቸው እንዲሁም በተሽከርካሪ ስምሪትና ቁጥጥር ስርዓት (e- Fleet Management)፣ ቅሬታ እና ጥቆማ መቀበያን ዲጂታላይ በማድረግ፣ በኤሌክትሮኒክ ትምህርት (e-Learning)፣ ዲጂታል ደብዳቤ (e- Lettering) ስርዓቶች ውጤታማ ሆነው እየተተገበሩ መሆናቸው ተጠቅሷ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀጣይ የትግበራ ምዕራፍ ላይ አስተዳደርና አደረጃጀት፣ ዘመናዊ የሰራተኞች መረጃ አያያዝ፣ ፍትሐዊና ተደራሽ የመንግስት ግዥ፣ ዲጂታል የመንግስት ግዥ፣ ብዝሃነትና አካታችነት፣ የሰራተኞች ብቃትና ምዘና ማረጋገጥ በሚቻልበተ ሁኒታ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተብራርቷል።

የክብርት ዋና ዳይሬክትሯን ገለጻ ተከትሎ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በዋና ዳይሬክተሯ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

በመጨረሻም በ2017 በጀት ዓመት ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ አመራሮች፣ ስራ ክፍሎች እና ሰራተኞች የእውቅና እና የምስጋና የምስክረ ወረቀት በማበርከት የዕለቱ መርሃግብር ተጠናቋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *