Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

ለምለሟ ምስራቅ ጉራጌ ሌላ ገፀ በረከት ተደረበላት።

(ሀምሌ 26/2017 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በክረምት ወራት የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራት ሲያከናውን የቆዬ ሲሆን በዛሬው እለት የባለስልጣኑ አመራርና ሠራተኞች  በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ ከ25000 በላይ ችግኞችን ተክለዋል።

በእለቱ ከችግኝ ተከላው በተጨማሪ ለ100 ተማሪዎች ሙሉ የመማሪያ ቁሳቁስ አበርክተዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰንን ጨምሮ የዞን፣ የወረዳ እና የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ከችግኝ ተከላው በኋላ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮሎጂን ለማስተካከልና የቱሪዝም ምህዳርን ለማስፋት ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንዳለው ያመላከቱ ሲሆን ዞኑ በትኩረት እየሰራ እንደሆነ አመላክተዋል።

የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው በክረምቱ ወራት በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል ችግኞች ሲተከሉ መቆየታቸዉን ጠቅሰው በዛሬዉ እለትም ከ25000 በላይ ችግኞችን ተክለናል ብለዋል። ክብርት ወ/ሮ መሰረት አያይዘውም ጉራጌ የሰላምና የታታሪነት ተምሳሌት የሆነ ማህበረሰብ መክተሚያ በመሆኗ በዚህ ቦታ አሻራችን በማሳረፋችን ደስ ይለናል ያሉ ሲሆን ችግኞችን ከመትከል በዘለለ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራም ገልፀዋል።

በመጨረሻም የባለስልጣኑ አመራሮች የትምህርት ቁሳቁሶችን ለተማሪዎች ያበረከቱ ሲሆን ለባለስልጣኑ አመራርም ከዞኑ ዋና አስተዳዳሪ የተለያዩ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *