Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።

(ሰኔ 19/2017 ዓ.ም )፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአሰራር ስርዓቱን ለማዘመንና ቅንጅታዊ አሰራርን ለማሳደግ በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማ ፒራሚድ ሆቴል ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል። 

በውይይቱ ላይ ባለስልጣኑ መስሪያ ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት የተተገበሩ አበይት ተግባራት በዋና ዳይሬክተሯ ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን የ2018 እቅድና እና ሌሎች የሪፎርም ስራዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ይሆናል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *