Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

በe-GP ሲስተም ትግበራ ዙሪያ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡

(ግንቦት18/2017 ዓ/ም) የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የe-GP ሲስተምን በሁሉም የፌደራል ተቋማት እና ቅርንጫፎቻቸው እንዲተገበር ማድረጉን ተከትሎ አዋጭነቱን በጥናት ጭምር በማረጋገጥ ወደ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ለማስፋት አቅዶ ግንዛቤ በመፍጠር ለተግባራዊነቱም እየተጋ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡

ይህን ጥረት ተከትሎ ተግባራዊ ካደረጉት መካከል አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቅቆ በባለስልጣኑ በተሰጠው ስልጠና እና ድጋፍ መነሻነት ተግባራዊ እያደረገ ለሌሎች ጭምር አርዓያ እየሆነም ይገኛል፡፡ ለዚህም በማሳያነት የተጠቀሰው የአዲስ አበባ ፋይናስ ቢሮ ግንባር ቀደም ሆኖ ተመርጧል፡፡

ቢሮው የተገበረበትን መንገድ በተሞክሮነት ለማጋራት በዛሬው ዕለት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የመጣውን ልዑክ ተቀብሎ ልምዱን አካፍሏል፡፡ በሂደቱም ስልጠናና ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የስራ ኃላፍዎችና የሲስተም ባለሞያዎች በጋራ በቢሮው ተገኝተዋል፡፡

ልዑኩን ተቀብለው ያነጋገሩት የአዲስ አበባ ፋይናስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ሲስተሙን ለመተግበር የሄዱበትን ሂደት አንድ በአንድ አብራርተው በሂደቱ ውስጥ ባለስልጣኑ የነበረው ሚና ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ ገልጸዋል፡፡

በመቀጠልም ቀደም ሲል ቢሮው ተግባራዊ ሲያደርገው የነበረውን የማንዋል የግዥ ስርዓት ለማዘመን የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓትን ለመተግበር አማራጭ ማድረጉን አስታውሰው ያለውን የአፈጻጸም ልዩነት ለልዑካን ቡድኑ ገልጸዋል፡፡ የቢሮ ኃላፊው አክለውም አሁን ላይ የኤሌክትሮኒክ ግዥ ትግበራ የሚገኙበትን ደረጃ እና የሄዱበትን የአሰራር ሂደት በማሳያነት አንስተው አብራርተዋል፡፡

በመቀጠልም ተሞክሮውን ለመውሰድ በቢሮ የተገኘው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ልዑክ በበኩሉ በአፈጻጸም ሂደቱ ግልጽነት ይሻሉ በሚሏቸው ጉዳዩች ዙሪያ ጥያቄዎችን ያነሱ እና ሀሳብ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄዎች የቢሮው ኃላፊውና የባለስልጣኑ የስራ ኃላፊዎች ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡

አያይዘውም በነበሩበት የትኛውም ሂደት የቢሮው የአፈጻጸም ሂደት እንዲሳለጥ ባለስልጣኑ ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን በድጋሚ ችረዋል፡፡
ቢሮዉ ለeGP ሲስተም ትግበራ ያዘጋጀውን ሠርቨር እና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎች ልዑኩ እንዲጎኘዉ በማድረግ መረሃ-ግብሩ ተጠናቋል፡፡

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *