Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

በ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።


(ሰኔ 13/2017 ዓ.ም)፣ የፌዴራል የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀማቸውን በጋራ ገምግመዋል።

የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱ በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱ  በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ አበይት የሪፎርም ስራዎች፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ጥራትና ቅልጥፍናን ለመጨመር የተተገበሩ የዲጅታል ስራዎች፣ ቅንጅታዊ አሰራር ውጤታማነትን ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎች፣ የሰው ሀይል ግንባታ ላይ የተከናወኑ አበይት ተግባራት፣ ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተወሰዱ የመፍትሔ አቅጣጫዎችና የተገኙ ውጤቶች በስፋት ተተንትነው ቀርበዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ አያይዘውም የ2018 በጀት ዓመት እቅድን ያቀረቡ ሲሆን እቅዱ የ2017  በጀት ዓመት ክንውንን መነሻ ያደረገና የተገኙ መልካም ውጤቶችን የምናስቀጥልበት በሌላ በኩል የነበሩብንን ክፍተቶች የምንሞላበት እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጄ ነው ሲሉ አብራርተዋል።

በተጨማሪም በውስጥ አቅም ለምተው ስራ ላይ የዋሉ ዲጂታል ስራዎች (website, e- learning, letter management, …) በኢጂፒ ፕሮጀክት ባለሞያዎች አማካኝነት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም የቀረቡትን ገለፃዎች መነሻ በማድረግ ከመድረክ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በክብርት ወ/ሮ መሰረት የማጠቃለያ እና የቀጣይ ስራ አቅጣጫ የዕለቱ መርሃ-ግብር ተጠናቋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *