Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

በፌደራል የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዐዋጅ ቁጥር 1333/2016 በተካተቱ አዳዲስ ይዘቶችና የተሻሻሉ ጉዳዮች ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

(ግንቦት 10/2017ዓ/ም) የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 1333/2016 የጸደቀውን አዲሡን አዋጅ ማስፈጸም የሚያስችሉ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያወችን እያዘጋጀ የቆየና ቀደም ሲል የራሱን ሠራተኞች ጨምሮ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት እያወያየ ገንቢ አሥተያየቶችን በማሻሻያነት እየጨመረ አዋጁን ለሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት በማስገምገም ግብዓት በማሰባሠብ አበልጽጎ የማስፈጸሚያ መመሪያዎችን አዘጋጅቷል።

ስለሆነም የተናበበና የተጣጣመ የግዥና ንብረት አስተዳደር ስርዓት እንዲኖር ሁሉም ክልሎች አዋጁን መሠረት ያደረገ መመሪያ አዘጋጅተው የአካባቢያቸውን ተጨባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት መሠረታዊ ህጉንና የአሠራር ሥርዓቱን ሳያዛቡ አዘጋጅተው እንዲተገብሩ እንደሚረዳ ታሥቦ መመሪያውን ከሚቀዱበት አዋጅ አኳያ የተካተቱ አዳዲስ ይዘቶችንና የተሻሻሉ ጉዳዮችን ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ለክልልና የከተማ መስተዳድር ቢሮ ኃላፊዎች በደብረ ዘይት ከተማ ፒራሚድ ሆቴልና ሪዞርት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነው።

በዐዋጁ የተካተቱ አዳዲስ ይዘቶችና የተሻሻሉ ጉዳዮች የመንግስት ግዥ ማሻሻያ አቅም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ በሆኑት አቶ መላኩ ተጓዴ የቀረበ ሲሆን በዋናነት አዲሡ አዋጅ ከነባሩ ያለውን ጉልህ ልዩነት በማሳየትና የተደረጉ መሠረታዊ ማሻሻያዎችና የተካተቱ አዳዲስ ይዘቶች ላይ ልዩ ትኩረቱን ያደረገ ማብራሪያ ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።

መሪ ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ክልሎች ከአዋጁ ጋር የተናበበና የተቀራረበ የማስፈጸሚያ መመሪያቸውን ሲያዘጋጁ ሀገራዊ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ የማስፈጸሚያ ህጎችን ባስጠበቀ መልኩ ስለሚሆን ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አጣጥመው መመሪያ አዘጋጅተው ለመፈጸም እንዲችሉ ስለሚረዳ የተሻሻሉ እና እንደ አዲስ የተካተቱ ይዘቶችን ልዩ ትኩረት ሠጥቶ
መረዳቱ አስፈላጊ መሆኑንን ተገንዝበው ሊሻሻል ይገባል በሚሉት ዙሪያም ሀሳብ አስተያየታቸውን ለተጨማሪ ግብዓትነት ሊሠጡ እንደሚገባ በገለጻቸው ወቅት አሳስበዋል።

በመቀጠልም ተሳታፊዎች ባለሥልጣኑ እየተገበረ ያለው መሠረታዊ ተግባሮች በቂ ዝግጅት የተደረገበትና ሀገሪቱን የሚመጥን
መሆኑን በአድናቆት በመግለጽ፤
ከህይወት ዘመን ወጭ ትንተና፣ከግልግል ዳኝነት፣ከቀጥታ ግዥ ፣ ከክዋኔ ኦዲት ጋርስ ተያያዥነነት ያላቸውና ሌሎች መሠል ጉዳዮችን ተጨማሪ ማብራሪያ ከሚሹ ሀሳቦች መካከል አንስተዋል።

በመጨረሻም የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ ለተነሱ ጉዳዮች የማጠቃለያ ምላሽና አስተያየት የሰጡ ሲሆን

በቀጣይ ባለስልጣኑ የተሻለ የግንኙነት መረብ እንዲፈጠር በማድረግ ለክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ልዩ ልዩ የአቅም ግንባታ ስራዎችና ሥልጠናዎች ላይ በማተኮር የአፈጻጸም ልዩነቶችን የማቀራረብ ተግባር ላይ አበክሮ እንደሚሠራ የገለጹ ሲሆን የምትሠሩባቸው ዘርፎች ከልማት እንቅስቃሴዎች ጋር በቀጥታ የተያያዙ መሆናቸውን በመገንዘብ የቀረበውን ገለጻ በዉይይት ማዳበራቸው የተሰጣቸውን ተግባርና ኃላፊነት ለመወጣት እንደሚረዳቸው ሙሉ ዕምነታቸውን ገልጸው ለተሻለ ተፈጻሚነት ከዚህም ባለፈ ባለስልጣኑ በየትኛውም ዘዴ የተለመደ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጭምር በመግለጽ ለዐዋጅ ማሻሻያው የተዘጋጀውን መርሃ -ግብር አጠናቅቀዋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *