Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

Author: Yonas Habesha

አረንጓዴ ዐሻራ ለአለም ምሳሌ የሆንበት ነው ። ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ

(ሀምሌ 24/2017 ዓ/ም)፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የከባቢ ለውጥን በመታደግና የአየር ንብረት ለውጥን በማስተካከል ለአለም ተምሳሌት ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ ገልጸዋል።

ክቡር አቶ አህመድ ይህን ያሉት የገንዘብ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በሸገር ከተማ አስተዳደር  ኩራ ጅራ ክፍለ ከተማ የችግኝ ተከላ መርሃግብር በአከናወኑበት ወቅት ነው። ክቡር አቶ አህመድ በንግግራቸው አረንጓዴ አሻራ የምግብ ዋስትናን በማረጋግጥ እና የወጣቶችን የስራ እድል በመፍጠር በኩልም ያለው አስተዋፅዖ የጎላ መሆኑን አመላክተዋል።

በሌላ በኩል ሸገር ከተማ አስተዳደር ካለው መሬት ውስጥ 30% በአረንጓዴ ተክሎች ለመሸፈን ከ2.8 ሚሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተው ወደ ተግባር መገባቱን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ዶክተር ተሾመ አዱኛ አስታውቀዋል፡፡

የችግኝ ተከላ መርሃግብሩ እንደ ሀገር የተያዘውን በአንድ ጀምበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል እቅድ አንዱ አካል ሲሆን በእለቱ ከ6000 በላይ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች ተተክለዋል።

በእለቱ ከችግኝ ተከላው በተጨማሪ ለ1350 ተማሪዎች ሙሉ የትምህርት ቁሳቁስ እና የ15 አረጋውያን ቤት ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ የመጣል ስራ የተከናወነ ሲሆን ለገንዘብ ሚኒስቴር እና ለግዥና ንብረት ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች ከክቡር ከንቲባው፣ ከአባገዳዎች እና ከአባቶች ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

#GreenLegacy

#700MillionTreesaday!

ሰውን የማገዝ ምንጩ ሰው መሆን ነው፡፡ ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ

(ሀምሌ 23/2017 ዓ/ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በያዝነው የክረምት ወቅት የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከአከናዎናቸው የበጎ አድራጎት ተግባራት አንዱ ማዕድ ማጋራት ሲሆን ዛሬ የባለስልጣኑን ዋና ዳይሬከተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌን ጨምሮ ሁሉም አመራር በመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር በመገኘት ማህበሩ እያከናወናቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶችን የመጎብኘት፣ ከ1000 በላይ አረጋውያን ማዕድ የማጋራትና  የማበረታታት ስራ ስርቷል፡፡

መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር በመላ ሀገራችን 46 ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን በአጠቃላይ ከ8500 በላይ አረጋውያንን፣ አቅመ ደካሞችንና ህሙማንን ተቀብሎ የሚያኖር፣ የሚንከባክብ፣ የሚያሳክምና የሚጦር ማህበር መሆኑ በጉብኝቱ ወቅት ተጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም በማህብሩ ውስጥ ማህበራዊ እና ሀይማኖታዊ ትውፊቶች ሳይቀር እኩል የሚስተናገዱበት ሂደት ኢትዮጵያን በአንድ ጣራ ስር እንድናያት የሚያደርግ እንደሆነ ተገለጿል፡፡

በማዕድ ማጋራቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬከተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ  በንግግራቸው መንግስት ፖሊሲ ቀርጾ ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች በምገባ፣ በትምህርት ቁሳቁስ፣ የአረጋውያንን ቤት በማደስ እና በመሳሰሉት ድጋፍ ማድረግ መሆኑን የገለጹ ሲሆን  ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ያደረገው ድጋፍም የዚህ አንድ አካል ነው ብለዋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ መሰረት በንግግራቸው ሰውን የመደገፍ ምንጩ ሰው መሆናችን በመሆኑ መቄዶንያን መደገፍ ሀገርን መደገፍ ነው ምክያቱም ኢትዮጵያን በትክክል ልናያትና ልናውቃት የምንችለው መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር ውስጥ ነው ሲሉ አክለዋል፡፡

በሌላ በኩል የማህበሩ መስራችና ስራ አስኪያጅ የክቡር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ላደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የሆነ ማህበር ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡ የክቡር ዶክተር ቢኒያም መቄዶንያ ምንም ሳይኖረው የተነሳ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ለምገባ በቀን ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ማህበር ነው፡፡ ይህ ደግሞ በቅን የኢትዮጵያ ልቦች የሚከናወን ነው በለዋል፡፡ የክቡር ዶክተር ቢኒያም አያይዘውም መቄዶንያ አሁን ላይ የሆስፒታል እና የአረጋውያን መጠለያን ጨምሮ ተደራሽነቱን ማስፋትም አስፈላጊ በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የድርሻውን ቢወጣ ስራዎችን ማቅለል እንችላለን ብለዋል፡፡

በእለቱ የግዥና ንብረት ባለስልጣን ባከናወነም መልካም ተግባር እለቱ በቋሚነት በባለስልጣኑ ስም እንዲታወስ በአረጋውያን የተጠየቀ ሲሆን ሀምሌ 23 በየአመቱ “የመልካምነት ቀን” ተብላ አረጋውያንን በመንከባከብና መልካም በማድረግ የምትታሰብ ይሆናል፡፡

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዚህ በፊትም የተለያዩ ድጋፎችን አድርጓል፡፡

ውጤታማ እቅድ የነገ ብሩህ መንፅር ነው፡፡

(ሀምሌ 20/2017 ዓ.ም)፣ ለመንግስተ ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው የእቅድ ዝግጅት፣ ክትትል፣ ግምገማ እና ሪፖርት አቀራረብ ስልጠና ተጠናቋል፡፡ ስልጠናው ሁለት ቀናትን የፈጀ ሲሆን የእቅድ አዘጋጃጀት፣ የግምገማ ስርዓትና ሂደት እንዲሁም ሪፖርት አቀራርብ ላይ የሚታዩ ክፍትቶችን ለመሙላትና በእቅድ ላይ የተመሰረት ተግባር ተኮር ውጤት ለማስመዝገብ ታስቦ የተዘጋጄ ነው፡፡

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱትና የስልጠናው አካል የነበሩት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ሲሆኑ የላቀ ውጤት እንዲመዘገብና የሚከናወኑ ተግባራት በስኬት እንዲጠናቀቁ እቅድ እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ መሰረት አያይዘውም ተቋማዊ ራዕይ እና አላማ ያለ እቅድ ሊሳካ የሚችልበት አግባብ ሊኖር እንደማይችልና የሚታቀድ እቅድም የታቀደበት ስለማይሆን በእቅዳችን ስኬት ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል፤ ስኬትም ከስኬታማ እቅድ ይመነጫል፡፡ ስለሆነም አሳታፊ እና ፈፃሚን የሚያነሳሳ እቅድ ማዘጋጀተት ብሎም እቅዳችን በየጊዜው መከታተልና መገመገም አሰፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ መሰረት በንግግራቸው እቅድ የተቋማዊ ስኬት መልህቅ አሊያም ነገን የምናይበት ብሩህ መንፅር በመሆኑ በትኩረት ልንሰራበት እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል እቅድን ማባከን ነገን ማባከን በመሆኑ ትክክለኛ እና እኛን የሚገልፅ እቅድ ማቀድና ክትትልና ግምገማ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ስልጠናውን የሰጡት አቶ ጀማል አህመድ ገልጸዋል፡፡ አቶ ጀማል አክለውም እቅድ የህይወታችን መንገድ በመሆኑ ነገን ስኬታማ ለማድረግ ዛሬ ስኬታማ እቅድ ማቀድ ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም እቅድ ማቅድ ብቻውን ስኬት የማያመጣ በመሆኑ የእቅድ ክትትል እና ግምገማ ማካሄድ ብሎም እንደ ተጨባጭ ሁኔታዎች መከለስ የሚያስፈልግ ይሆናል ብለዋል፡፡

ደሜን ለወገኔ የደም ልገሳ መርሃግብር ተከናወነ፡፡

(ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራትኞች በክረምት ወራት ከዋናው ስራቸው ጎን ለጎን የተለያዩ የብጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዚህም በእንጦጦ እና በላፍቶ ለሶስት ጊዜያት የችግኝ ተከላ መርሃግብር ያከናወኑ ሲሆን በዛሬው እለትም “ደም በመለገስ ህይወትን እንታደግ” በሚል መሪ ቃል የደም በመለገስ መርህግብር አከናውነዋል፡፡

በቀሪ የክረምት ወራትም የችግኝ ተከላ፣ የምገባ፣ አቅመ ደካሞችን የማገዝና ሌሎች የበጎ አድራጎት ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ ሲሆን ይህ የደም ልገሳ መርሃግብርም የክረምቱ የበጎ አድራጎት አንዱ አካል ነው።