Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

የፊደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የባለስልጣኑን የዝግጅት ምዕራፍ የሪፎርም ስራዎችን ገመገመ፡፡

(ግንቦት19/2017ዓ/ም) በመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ስርዓት ውስጥ በየዘርፉ የሚስተዋሉ የአሰራር ማነቆዎችን ነቅሶ በማውጣት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት የሚያስችለው ፖሊሲ ከመጽደቁ በተጫማሪ ከፖሊሲው የሚቀዳ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር የሪፎርም ስራ ተቀርጾ ወደ ትግበራ መገባቱ ይታወቃል፡፡

ሪፎርሙን በውጤታማነት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የሪፎርም ትግባራ የሚመራበት አግባብ፣የትግበራ ምዕራፎችን እና የሚከናወኑ ተግባራትን በግልጽ የሚያመላክት እና አቅጣጫ የሚጠቁም ፍኖተ ካርታ ጭምር ተዘጋጅቶለት ለተግባራዊነቱ ወደ ተቋማት ወርዷል፡፡

ይህንን ሃገራዊ ተልዕኮ ለማስፈጸም ከተመረጡት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የዝግጀት ምዕራፉን በተሻለ አፈጻጸም አጠናቋል፡፡ ይህን ተከትሎ በዛሬዉ ዕለት ትግበራዉን ለመደገፍ እና ለመቆጣጠር ኃላፊነት የተሰጠው የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ልዑኩን ለዚሁ የሪፎርም ስራዎች የዝግጀት መርሃ-ግብር ግምገማ በስፍራው አሰማርቷል፡፡

ልዑኩን ተቀብለው ያነጋገሩትና የተጠናቀቀዉን የዝግጅት ምዕራፍ የሪፎርም ስራዎች እንዲገመግም ተግባራቱን አደራጅተው የጠበቁት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ በሪፎርም ስራዎች የተከናወኑ ተግባራትን አንድ በአንድ በሰነድ ማስረጃዎች ጭምር በማስደገፍ በገለጻቸውን አቅርበዋል፡፡

በዝግጅት ምዕራፍ ከተተገበሩት የሪፎርም ስራዎች ውስጥ በዋናነት የተቋሙን ዌብሳይት፣ የe-learning የመማሪያ ስርዓት፣ዘመናዊ የደብዳቤ ልዉዉጥ ስርዓት( Letter management system)በራስ አቅም አልምቶ መተግበሩ፣የነዳጅ አጠቃቀምና የተሸከርካሪ ስምሪት (e-fleet management)፣እየተዘጋጁና እየተተተገበሩ የሚገኙ መመሪያዎች፣አዋጁን አካታች ለማድረግ በምልክት ቋንቋ እና በብሬል ጭምር በማሳተም የተሰሩ ተግባራት፣ ለሴቶች እና ህጻናት እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች ልዩ ትኩረት በመስጠት የተተገበሩ ምቹ የስራ አካባቢን የመፍጠር ትግበራዎች፣ የe-GP ሲስተምን ተጠቃሚ ተቋማት የማስፋት እና የሲስተም ማሻሻያዎችን የማከናዎን ተግባራት፤የሲስተም ትስሰር ከሌሎች ተቋማት ጋር መፈጠሩ፤ተገልጋዩች ባሉበት ሆነው እገዛ የማግኘት፤ቅሬታ የማቅረብ እና ምላሽ የመቀበል አሰራርን ያካተተ የሲስተም ማሻሻያ ትግበራ መዘርጋቱ፣የተገልጋዩች ቻርተር መዘጋጀቱ፣ ልዩ ልዩ የአቅም ግንባታና ሙያዊ ስልጠናዎችን እንዲሁም ሌሎች ሰፊ የሪፎረም ስራዎች መከናወናቸውን በገለጻቸው አካትተዉ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የሠነድ ማረጋገጫ ጭምር በማቅረብ አሳይተዋል፡፡

ልዑኩ በቀረበው ገለጻ ላይ ተመርኩዞ በተግባር ማየት የሚፈልጋቸውን ሁሉም ሰነዶች ቀርበውለት የተመለከተና በተጨባጭ መተግበሩን ጭምር ለማረጋገጥ ተዘዋሮ በመጎብኘት ያረጋገጠ ከመሆኑም ባሻገር በአፈጻጸሙ እጅግ ደስተኞች መሆናቸውን በማስቀደም፤ በተለይም ለሰራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር የተሄደበት እርቀት እና አገልግሎት አሰጣጡን ከማዘምን ጋር የተያያዙት ትግበራዎች ልዑኩ ከተሰማራበትና ልዩ ትኩረቱን አድርጎ ከሚገመግመበት አጀንዳዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለዉ ጥሩ አፈጻጸም መሆኑን አበክረዉ ገልጸዋል፡፡

በመቀጠልም በልዩነት ሴት ሰራተኞችን ለመደገፍ እና ለማብቃት እየተከናወነ ያለው ቁልፍ ተግባር፣ ሠራተኞች ያለችግር ልጆቻቸው እየተከታተሉ እንዲሰሩ የተዘጋጀው የህጻናት ማቆያ፣ አዋጁን አካታች ለማድረግ የተሄደበት እርቀት (ብሬልን እና የምልክት ቋንቋን መጠቀሙ)፤ድህረ-ገጽ እና የe-learning ፕላትፎርም በራስ አቅም አልምቶ ወደ ተግባር መገባቱ እና አሰራርን በተለይም የግዥን ስርዓቱን ለማዘመን የተፈጸሙ ተግባራት ይበል የሚያሰኝ እና ለሌሎች ተቋማት ጭምር ለማሳያነት ሊውል የሚችል መልካም አፈጻጸም የታየበት ድንቅ ተግባር ነው ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ልዑኩ በተገኘበት ወቅት የገንዘብ ሚኒስቴር ልዑክም እንደ ተጠሪ ለመደገፍና ለመከታተል በስፍራው ተገኝቷል።

በመጨረሻም የተከናወኑ ተግባራትን ተጨባጭነት ለማረጋገጥ የህጻናት ማቆያዉን ጨምሮ ሁሉንም የስራ ክፍሎች ተዟዙረዉ ጎብኝተው የግምገማ መረሃ-ግብሩ ፋጻሜውን አግኝቷል፡፡

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *