Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

የሴት ሰራተኞች የፎረም አመራርና አባላት የውይይት መድረክ አካሄዱ፡፡

(ሰኔ 7/2017) በቢሾፍቱ ከተማ ፒራሚድ ሆቴል በተዘጋጀው መድረክ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ሴት ሠራተኞች ፎረም አመራር እና አባላት በፎረሙ ህገ-ደንብና በቀሪ ወራት ዕቅድ ዙሪያ ተወያይተው ለተፈጻሚነት ለማጽደቅ ያለመ መድረክ ነው፡፡

በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌን ጨምሮ ሁሉም ሴት ሰራተኞች እና የፎረሙ ተባባሪ አባል የሆኑ ወንድ ሠራተኞች የተሳተፉ ሲሆን የፎረሙን የመመስረቻ ህገ-ደንብ እና የቀሪ ወራት ዕቅድ ለአባላት ቀርበው እና ተወያይተውበት ለግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦች ተነስተዋል፡፡

የተነሱ ሁሉም ግብዓቶች ተካተውበት የተቋቋመበትንም ዓላማ ለማሳካት የሚመጥን ህገ-ደንብ ተዘጋጅቶለት ለአፈጻጸም በሚያመች መልኩ ህገ-ደንብ ማውጣት አስፈላጊ በመሆኑ ለተነሱ ሃሳቦች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶበት እንደሚሻሻል የጋራ ስምምነት ተደርሶበት ህገደንቡም እቅዱም በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡

በመጨረሻም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በንግግራቸው ፎረሙ ሴቶች እርስ በእርስ የሚመካከሩበት፤ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት የሚያጋጥማቸውን እንቅፋቶችም በግልጽ የሚነጋገሩበት ብሎም ነጻ ጊዜ የሚያገኙበት እና ማህበራዊ ግንኙነታቸውን የሚያዳብሩበት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው እና እንደ ተቋምም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዕድል የሚሰጥ ትልቅ ሚናን የሚጫወት በመሆኑ ተቋሙ ሴት ተኮር ስልጠናዎችን፣ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ስራዎችን ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ሠራተኞች ከሚመለከታቸው አደረጃጀቶች ጋር ግንኙነት ፈጥሮ ማመቻቸት እና ቅድመ ስልጠናዎችን ማዘጋጀት፤በጥቅሉ ሴቶች በስነ-ልቦና፤በኢኮኖሚ፤በፈጠራ ችሎታቸው የተሻሉ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ የትኛውንም ተቋማዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመቀጠልም ዋና ዳይሬክተሯ በአስተሳሳብ እና በአመራር ብቃት የተለወጡ መሪዎችን ለማፍራት አጋዥ የሆነውን በሣይንሳዊ ጥናት ተደግፎ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የስራ አመራር እና መሪነት መካከል ያለውን ልዩነት እንዲሁም የመሪነት አስፈላጊነት፤ታሪካዊ የዕድገት ደረጃዎች፤ዘይቤና ክህሎቶች፤ዋና ዋና ተግባራትና መርሆች እንዲሁም ዘመናዊ የአመራር አስተሳሰቦች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ገለጻ ተሰጥቶበታል፡፡

በመጨረሻም ተሳታፊዎች በቀረበው ስልጠና ዙሪያ ሃሳብ አስተያየቶችን በሰፊው በመስጠት የዕለቱን መረሃ- ግብር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *