Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

ከሕዝብ ተወካዩች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ እና ከፌደራል ዋና ኦዲተር ኃላፊዎች ጋር በነበረው የውይይት መድረክ የተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች፤ሃሣብ እና አስተያየቶች ከተሰጡ ማጠቃለያዎች ጋር

(ግንቦት20/2017ዓ/ም) ከቀረበው ሰፊ ገለጻ በኋላ በሁለቱም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና አባላት እንዲሁም የፌደራል ዋና ኦዲተር የስራ ኃላፊዎች ግልጽነት የሚሹ ጥያቄዎች እና ሃሳብ አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡

ዕድሉን የወሰዱ ተሳታፊዎች የኢጂፒ ሲስተም በሁሉም የፌደራል ተቋማት እና በ93 ቅርንጫፎቻቸው ከመስፋፋቱም ባለፈ ለሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ጭምር ለተሞክሮ ማጋሪያነት መዋሉ፣ሪፎርሙን ከአዋጅ ጋር አስተሳስሮ መተግበሩ፣ አዋጅ ቁጥር (1333/2016) ለማስተግበር የሚያስችሉ የተለያዩ መመሪያዎችን ለማዘጋጀት የተደረገው ጥረት፣ የአዋጁን አካታችነት እና ተደራሽነት ለማሳለጥ በምልክት ቋንቋና በብሬል ጭምር መታተሙ፣ በአመራሮች እና ባለሙያዎች ላይ የነበረው ቁርጠኝነት፣ በመርህ ደረጃ የሚወሩ ህጎችን በተግባር ለማሳየት የተደረገው ጥረት እና መሠል ጉዳዮች በአዎንታዊነት ከተነሱት መካከል ይገኙበታል፡፡

ከሲስተሙ ጋር ተያይዞ ከደህንነት ፖሊሲ፣ነጋዴው ማህበረሰብ ሲስተሙን መጠቀም እንዲችል ግንዛቤ ከማሳደግ ጋር በተያያዘ፣ የተጠቃሚዎች የእርካታ ዳሰሳ ከመተግበሩ ጋር የተያያዙ፣ ከሲስተም ትስሰር እና ቴክኖሎጂውን ከሚያስተዳድር የስራ ክፍል ጋር የተያያዘ እና መሰል ጉዳዩች ግልጽነትት ከሚሹት ጎራ ተነስተዋል፡፡

ከአጠቃላይ የተቋሙ የስራ እንቅስቃሴና አዲሱ አዋጅ ጋር በማስተሳሰር ከተነሱት መካከል ደግሞ አዋጁን ለማስፈጸም የሚዘጋጁ መመሪያዎች መዘግየት፤ የደንብ አለመወጣት፣ የሚያስፈልጉ ማሻሻያዎችን አጥንቶ ከማቅረብ አኳያ እና መሰል ተያያዥ ጉዳዩች ምላሽ ከሚሹት መካከል ይገኙበታል፡፡

በመቀጠልም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ የመድረኩ ዋና ዓላማ እየሰራን ያለውን ገልጸን የሚሰጡ ሃሳቦችን ወስዶ ለማሻሻል ስለሆነ የተነሱ ሃሳቦችን በግብዓትነት የምንወስድ ሲሆን በቀጣይ ወደ ዕቅድ በመቀየር ተግባራዊ እናደርጋቸዋለን ብለዋል፡፡

አያይዘውም የተሰጡ አዎንታዊ አስተያየቶች በሙሉ ውጤታቸው የተመዘገበው በአመራሩ ቁርጠኝነት ብቻ ሳይሆን ሲስተም ካለማው አካል ጀምሮ ባለሙያዎች በኃላፊነት ስሜት ያከናወኗቸው ተግባራት የጋራ ድምር ዉጤት በመሆኑ አድናቆቱ ለሁሉም ይድረስ ሲሉ ተሰምተዋል፡፡

አያይዘዉም ለተነሱ ሀሳብ አስተያየቶች ጥቅል ተቋማዊ ምላሽ የሰጡ ሲሆን በተለይም ኢጂፒ ሲሰተም ሙሉ በሙሉ ሊያስገኝ የሚገባው ጥቅም እንዲስያገኝ ከማድረግ አኳያ፣ተቋማት የግዥ ስራዎችን ከሲስተሙ ጋር አስተሳስረው እንዴት እየተገበሩ እንዳለ የመደገፍ ሂደት ላይ፣ከሲስተሙ ደህንነት ፣ለንግዱ ማሀበረሰብ ሊሰጥ ከሚገባዉ ግንዘቤ የማሰጨበጥ ተግባር፣አዋጁ መመሪያ እንዲወጣላቸው በሚፈቅድላቸው ጉዳዩች ላይ መመሪያዎችን በማውጣት ረገድ፣ የባለስልጣኑን ድጋፍ በሚሹ በሁሉም ተቋማዊ ጉዳዮች፣የፌደራል ቅርንጫፍ መ/ቤቶችንና ክልሎችን ወደ ሲስተሙ በማስገባት ረገድ እና መሰል ተግባራት ላይ ቅድሚያ ተሰጥቶት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም በህዝብ ተወካዩች ም/ቤት የፕላንና ልማት እና ፋይናስ ጉዳዩች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ በማጠቃለያ ንግግራቸው ምክር ቤቱ አዋጁን ከማዘጋጀት እና ከማጽደቅ ባሻገር የመከታተል እና መተግበሩን የማረጋገጥ ድርሻ ያለው መሆኑን አስታውሰው ጸድቆ ወደ ተግባር በተለወጠው አዋጅ ደስተኞችና እንደ ሃገርም ተጠቃሚ ሆነናል ብለዋል፡፡

አክለውም ከአዋጁ መጽደቅ በኋላ ትግበራውን የማወቅ ፍላጎት እንደነበራቸዉ ገልጸዉ በዚህ የውይይት መድረክ ያለበት የትግበራ ሂደት ይበልጥ ግልጽ የሆነላቸዉ መሆኑን በማሰቀደም ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል በሚሉት ሁሉም ጉዳዩች የግዥዉ ዘርፍ የሃገሪቱን ከፍተኛ በጀት የሚይዝ እንደመሆኑ መጠን ትልቁን ሃላፊነትና የማስፈጸም ድርሻ የተሰጠዉ ባለስልጣኑ ዘመናዊ አሰራርን በሃገራችን ተግባራዊ ከማድረግ ባለፈ ዓለምአቀፍ የገበያ ትስስር እንዲፈጠር በማድረግ ረገድ ሊተጋ ይገባል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ለተሻለ ለዉጥና ተጠቃሚነት በሚያስፈልጉ ማሻሻያዎች ዙሪያ ጥናት በማድረግ ቢመጣ በም/ቤቱ በኩል ማሻሻል የሚቻልበት አግባብ መኖሩን በመጠቆም የዉይይት መርሃ- ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *