የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከገንዘብ ሚኒስቴርና የገንዘብ ሚኒስቴር ተጠሪ ከሆኑት ተቋማት ጋር በመሆን በዓለም ለ110ኛ ጊዜ በኢትየጵያ ደግሞ ለ45ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የሴቶች ቀን "መብት የሚያስከብር ማህበረሰብ እንገንባ” በሚል መሪ ቃል የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አዳራሽ በድምቀት አከበረ፡፡
ክብርት ያስሚን ወሃብረቢ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በመክፈቻው ንግግር ላይ እንደተናገሩት ሴቶች በሀገራችን ላይ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ እንዳለ ገልጸው፣ በተለይ ባለፉት ሶሰት የለውጥ ዓመታት ሴቶች በሃገሪቱ ወሳኝ በሆነ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎአቸው በእጅጉ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡በመቀጠልም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ማርች 8 የሴቶችን የትግል ታሪክ፣ ሴቶች በቆራጥነት ያገኙትን ድል የምናሰታውስበትና የመጪው ዘመን ትግል በይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚደረግበት ዕለት መሆኑን አሰረድተዋል፡፡በዚህ የሴቶች ክብረ በዓል ላይ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን እና አካል ጉዳተኞችን አስመልክቶ ለተሳታፊዎች የግንዘቤ ማስጨበጫ በባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡ በመጨረሻ ይህንን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የእንጦጦ ፓርክ የጉብኘት ፕሮግራም ተካሄዷል፡፡ ለአንድ ቀን በቆየው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ክብረ በዓል ላይ ከተሳታፊዎች አሰያየቶች ተሰጥተዋል፡፡
የፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት