The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀንን አከበረ


የፌዴራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትርና ከመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጋር በመተባበር ለ9ኛ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ቅጥር ግቢ ዉስጥ ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. በተለያዩ ፕሮግራሞች በድምቀት አከበረ፡፡በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር የህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዋሲሁን  አባተ በዕለቱ በበዓሉ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ፡- “እኛ ኢትዮጵያውያን የድህነትና ኋላ-ቀርነት ታሪክ ከሀገራችን ተወግዶ፣ኢትዮጵያችን በልማትና በዴሞክራሲ ጎዳና በፍጥነት ተራምዳ ሩቅ በማይባል ጊዜ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ተርታ ትሰለፍ ዘንድ የጀመርነውን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ወደ ማይቀለበስ ደረጃ  እንዲደርስ፤ ሁለንተናዊ መዋቅራዊ ለውጥ በማረጋገጥ ሂደት ላይ የሚታዩ የመልካም አስተዳደርና የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋዎች በማስወገድ  ሁለተኛውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዳችንን ለማሳካት በሀገራችን ሰንደቅ አላማ ፊት ቆመን ቃል-እንገባለን” የሚለውን ቃለ- መሐላ በዓሉን ለማክበር ለተሰበሰቡት የሦስቱ ተÌማት ሠራተኞች ፊት ቆመዉ መላዉን ሠራተኛ ቃል አስገብተዋል፡፡መቀጠልም የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በበዓሉ ታዳሚዎች፣በፌደራል ወታደሮች እና  በድምፅ በተቀነባበረ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር በመታጀብ ባንዲራውን የመስቀል ሥነ-ስርዓት ተከናውኗል፡፡በጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም የተከበረውን የብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን የሶስቱም መ/ቤት ሠራተኞች በድምቀት አክብረዋል፡፡
ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ኤጀንሲዉ የመ/ቤቶችን ግዥ ሂደት መለካት ሊጀምር ነዉ

የመንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶችን የግዥ ሂደት መለካት የሚያስችል የግዥ መለኪያ መሣሪያ (key performance indicators guide line tools) በማዘጋጀት ወደ ስራ ለመግባት ዝግጀት ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡
የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ም/ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጆንሴ ገደፋ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ ሰፋፊ መሰረተ ልማትና ትላልቅ ግዥ የሚፈፀምባቸዉ የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች የተዉጣጡ በግዥ ላይ የሚሰሩ ኃላፊዎች፣የዉስጥ ኦዲት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር አዳማ በሚገኘዉ ሪፍት ቫሊይ ሆቴል ለሁለት ቀናት በቆየዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ እንደገለፁት የመንግስት ግዥ ከአገሪቱ አመታዊ በጀት ዉስጥ ከ60% እስከ 70% የሚሆነዉ ገንዘብ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ በመንግስት ግዥ ሥራ ላይ ስለሚዉል ኤጀንሲዉ የመንግስት ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ ብቻ ለማዋል እንዲቻል የመንግስት ግዥ ግልፅ፣ ቀልጠፋ፣ዘመናዊ፣ዉጤታማ፣ ከአድሎ ነጻ እንዲሁም ተጠያቂነት ያለበት በመሆኑ በሁሉም የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች፣ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ መስተዳደሮች ከ2009 በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ሲለሚሆን ልዩ ትኩረት ሠጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የመንግስት ግዥ መለኪያ መሣሪያዉ (key performance indicators guide line tools) ለሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ መስተዳደሮች በራሣቸዉ ነባራዊ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲያደርጉ የተደረገ ሲሆን ከሰፋፊ መሰረተ ልማትና ትላልቅ ግዥ ከሚፈፀምባቸዉ መ/ቤቶች የተዉጣጡ ኃለፊዎችና ባለሙያዎች ጥያቄዎች ተነስተዉ ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች መልስ በኤጀንሲዉ ምክትል ዋና ዳይሬክተር መልስ ተሠጥቷል፡፡
ሰፋፊ መሰረተ ልማትና ትላልቅ ግዥ ከሚፈፀምባቸዉ የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች የተዉጣጡ በግዥ ላይ የሚሰሩ ኃላፊዎች፣ የዉስጥ ኦዲት ኃላፊዎች እና የግዥ ባለሙያዎች የግዥ መለኪያ ዘዴዉ (key performance indicators guide line tools) ቀለል ብሎ የተዘጋጀና ከዕለት ዕለት ስራችን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለዉ መሆንና ተባብሮ ለመስራት ቁርጠኛ መሆንና ኤጀንሲዉ ሊመሰገን እንደሚገባና ለቀጣይ ስራቸዉ የግዥ መለኪያ መሣሪያዉ አጋዥ እንደሚሆንላቸዉ አያይዘዉ ገልፀዋል፡፡
ለሁለት ቀን በቆየዉ ግዥ መለኪያ መሣሪያ (key performance indicators guide line tools) የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ ከመ/ቤቶቹ የኦዲት ኃላፊዎች ጋር ትኩረት በመስጠት ለጋራ ዓላማ ኤጀንሲዉ ክትትል፣ቁጥጥር እና ድጋፍ ለማጠናከር ተባብሮ ስለሚሠራ ለሚዘገዩ የግዥ ፕሮጀክቶችና ለሚጓተቱ ግዥዎች መፍትሄ ይሆናል ተብሎ ይታመናል፡፡

በመንግስት የፋይናንስ፣ግዢና ንብረት አስተዳደር ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው

የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ እና የግዥ ንብረት አስተዳደር ላይ ያተኮረ ስልጠና በሀገሪቱ ውስጥ ለሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች እና ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ለተውጣጡ ባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እያካሄደ ነው፡፡
የመንግስት ወጪ አሰተዳደር ቁጥጥር ሪፎርም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሳ መሐመድ እንደተናገሩት በመንግስት ወጪ አሰተዳደርና ቁጥጥር ሪፎርም ፕሮግራም ለረዥም አመታት በተበታተነ መልኩ ሲሰጡ የነበሩ ስልጠናዎችን በተቀናጀ ሁኔታ ወደ ተቋማዊ በሆነ መንገድ በመቀየር በተከታታይነት ስልጠናዎችን ለመስጠት ያስችላል፡፡የዚህ ስልጠና ዋነኛ አላማ የመንግስት ፋይናንስ አሰተዳደርን አቅም ግንባታ በማሳደግ የመንግስት የፋይናስ አሰተዳደርን ይበልጥ ቀልጣፋና ውጤታማ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡ የስልጠናው ትኩረት በመንግስት የፋይናስ አሰራር፣በጥሬ ገንዘብና የክፍያ አፈጻጸም፣በመንግስት ግዢና ንብረት አሰተዳደር እንዲሁም በውስጥ ኦዲት ቁጥጥር ላይ ያተኮረ ነው፡፡በሌላ በኩል በአዲሱ የፋይናንስ አሰተዳደር አዋጅና በፋይናንስ ግልጽነትና ተጠያቂነት ዙሪያ ላይ ባለሞያዎቹ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ይደረጋል ሲሉ ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ስቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙሉጌታ ደበበ የሚሰጠው ስልጠና ባለሞያዎች በመንግስት ፋይናንስ አሰተዳደር ላይ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ይደረጋል ብለዋል፡፡
ስልጠናው ከ33 ዩኒቨርሲቲዎችና ስምንት የመንግስት ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ከ300 በላይ ባለሞያዎች በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ስልጠናው በአራት ዙሩች እንደሚቀጥልም ታውቋል፡፡
ምንጭ፡-Ministry of Finance and Economic Cooperation of Ethiopia's photo.

ኤጀንሲዉ የተቆጣጣሪነት ሚና ካላቸዉ ተቋማት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ ተፈራረመ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በሐምሌ 26/2008 ዓ.ም ከፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት እና ከኢትዮጵያ ግንባታ ፕሮጀክቶች መረጃዎች ተደራሽነት(CONSTRUCTION SECTOR TRANSPARENCY INITIATIVE-ETHIOPIA (COST-ETHIOPIA)) ጋር በጋራ ተባብሮና ተደጋግፎ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የየተÌማቱ ኃላፊዎች በተገኙበት በካፒታል ሆቴል ተፈራርመዋል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ አበበ እንደተናገሩት ከአገሪቱ በአመት በጀት ዉስጥ ከ60% እስከ 70% የሚሆነዉ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ በመንግስት ግዥ ሥራ ላይ እንደሚዉልና ከዚህ ዉስጥ ለግንባታ ፕሮጀክቶች የሚመድበዉ በጀት ደግሞ ከፍተኛ በመሆኑ በጋራ አብሮ መስራቱ የተሻለ ዉጤት እንደሚያመጠና ኤጀንሲዉ ስምምነት ሰነዱን(MEMORUNDUM OF UNDERSTANDING) ሲፈርም በሙሉ ፍቃደኝነትና ፍላጎት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አቶ ፀጋዬ አበበ አያይዘዉም የህዝብ ሃብት ለታለመለት ዓላማ እንዲዉልና በኢትዮጵያ የሚሰሩትን የግንባታ ፕሮጀክቶች ለህዝብ ይፋ በማድረግ የሚሰሩትን የግንባታ ፕሮጀክቶች ግልፅነትና ተጠያቂነት ማስፈን እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
በስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓቱ(MEMORUNDUM OF UNDERSTANDING) ላይ የተገኙት የፌዴራል ስነ ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አሊ ሱሌይማን፣ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት እና ከኮስት ኢትዮጵያ(CONSTRUCTION SECTOR TRANSPARENCY INITIATIVE - ETHIOPIA ወይም COST-ETHIOPIA) የተገኙ ኃላፊዎች አብዛኛዉ በአገሪቱ ዉስጥ የሚከናወኑ የግንባታ ፕሮጀክት ስራዎችን ግልፀኝነትንና ተጠያቂነትን ለማስፈን የግዥ ሂደቱን ለህዝብ ይፋ በማድረግ ህብረተሰቡ ጠያቂ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት የጋራ ስምምነት ፊርማዉ ትልቅ ዕገዛ እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል፡፡
ከኤጀንሲዉ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

የ2008 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2009 ዕቅድን በሚመለከት ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለመላው የኤጀንሲው ሠራተኞች የ2008 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና እና የ2009 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ሐምሌ 22 ቀን 2008 ዓ.ም በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚ/ር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡
አቶ ፀጋዬ አበበ የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የውይይቱ ዓላማ የ2008 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን መገምገም፣ የ2009 በጀት ዓመት ዕቅድንና መደበኛ ሥራዎችን በተመለከተ ውይይት እንደሚደረግ ገልፀዉ፣ የውይይቱም ተሳታፊዎች ጥያቄ በመጠየቅና አስተያየት በመስጠት በንቃት እንዲተሳፉ አሳስበዋል፡፡
በመቀጠልም የመንግስት ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ አሰራሮችን ከሪፎርምና ከመልካም አስተዳደር ተግባራት ጋር በማስተሳሰር ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ሙስናን የመከላከል ሥነ-ምግባርን በሚመለከት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት በ2ኛው የአምስት ዓመት ስተራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ መሠራት እንዳለበት  ገልጸዋል፡፡
በኤጀንሲው ውስጥ ያሉ የእያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሮች የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር በተመለከተ የመንግስት ገንዘብ ተመጣጣኝ ዋጋ ማስገኘት እንዲያስችል እና በዘርፉ መልካም አስተዳደርን ለማረጋገጥ ግልፅ ፣ፍትሀዊና በውድድር ላይ የተመሰረተ የመንግስት ግዥ አፈጻጸምን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲሁም የመንግስት ንብረት አስተዳደር ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ አሰራሮችን ከተÌማዊ ለውጥና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ጋር በማስተሳሰር ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም የ2008 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን፣ የ2009 በጀት ዓመት ዕቅድንና የመደበኛ ሥራዎች አፈፃፀምን በአራቱ ዕይታዎች ከተገልጋይ፣ ከፋይናንስ፣ ከውስጥ አሠራር፣ ከመማማርና ዕድገት እይታዎች አንጻርና እንዲሁም ሰለአጋጠሙ ችግሮችና ስለተወሰዱ የማስተካከያ አሰራሮች ገለጻ አድርገዋል፡፡
በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ በተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎ የጋራ ግንዛቤ ተወስዷል ፡፡
ለአንድ ቀን በቆየው የ2ዐዐ8 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2009 ዕቀድ  ውይይት ላይ የኤጀንሲው የበላይ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት