The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

ሙስና በአገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደረሰውን ተፅዕኖ በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

የፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከፌደራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ሙስና በአገራችን ኢኮኖሚ ላይ እያደረሰ ያለው ተፅዕኖ እና መወሰድ ስለሚገባቸው የመፍትሔ እርምጃዎችን በሚመለከት ለኤጀንሲው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ህዳር 27/2011 ዓ.ም. በመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት  የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዉስጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡

አቶ ፍሬሁን መለስ በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የፊት ለፊት ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ ሥልጠናውን የሰጡ  ሲሆን፣ ሙስና ምንድነው ከሚለው ተነስተው ሙስና ህግና ሥርዓትን ተከትሎ ከመስራት ይልቅ ስልጣንና ኃላፊነትን መከታ በማድረግ ህግና ሥርዓትን በመጣስ የመንግስትና የህዝብ ሃብትና ንብረትን መስረቅ፣ መዝረፍ፣ ማጭበርበር እንዲሁም በጉቦ፣ በዝምድና፣ በትውውቅ በጐስኝነት፣ በፖለቲካ ወገንተኝነትና በኃይማኖት ትሥሥር በመመርኮዝ ፍትህን አያዛቡ የግል ጥቅምን ማካበትና ሌላውን ወገን ተገቢ ባልሆነ መንገድ መጥቀም ወይም መጉዳት መሆኑን ስረድተዋል፡፡በመቀጠልም አሰልጣኙ የሙስና ወንጀል ልዩ ባህሪያትን ሲገልጹ የአፈፃፀሙ ሂደት እና ሥልት፣ለጉዳዩ ባለቤት ነኝ ባይ አለመኖር፣ የፈፃሚዎቹ ማንነት እና ምርመራውን ለማኮላሸት እና መርማሪውንም ሆነ ከምርመራው ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግለሰቦች ለማጥቃት መቻላቸውና በሕዝቡ ዘንድ እንደ ነውር አለመታየቱ እና ሙስናን በመዋጋት ተግባር ላይ የተሰማሩትን ሰዎች ማሸማቀቁ መሆኑን፣ እንዲሁም የሙስና ዓይነቶች ዝቅተኛ፣ከፍተኛ እና ፖለቲካዊ ሙስና መሆናቸውንና መገለጫቸውም ጉቦ፣ ምዝበራ፣ ማጭበርበር፣ በዝምድና እና በወዳጅነት መሥራት/አድሎ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመጨረሻም ሙስና ዓለም አቀፍ ወንጀል እንደሆነና በመንግሥት መ/ቤትና  ሕዝቡ ውስጥ በተወሸቁ ዘራፊዎች ትብብር የሚፈጸመው ይህ አስከፊ ወንጀል ዜጎችን እርቃን የሚያስቀር፣ ጥቂቶችን የሚያበለፅግ፣የመንግሥትን ተዓማኒነት የሚሸረሽርና ሕዝብን የሚያማቅቅ አደገኛ ችግር እነደሆነና ከዚህ አንፃር በአገራችንም ዓይነቱና መጠኑ ቢለያይም ወንጀሉን በጥብቅ መታገል ካልተጀመረ ከፊት ለፊት የተደቀነው አደጋ የከፋ መሆኑን አስረድተዋል፡፡በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ለአንድ ቀን በቆየው በሙስና ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ የኤጀንሲው ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

የፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ኤጀንሲው በ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ከመላው ሠራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ ከመላው የኤጀንሲው ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ጋር ህዳር 4 ቀን 2011 ዓ.ም በመንግስት ግዥና ንብረት ማሰወገድ አገልገሎት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ–ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የስብሰባው ዓላማ በዚህ በ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ምን አቅደን? ምንስ ፈጸምን? የሚለውን ለመወያየትና በቀጣይ መሰረት ለማስቀመጥ መሆኑን ለተሰብሳቢዎች ገልጸዋል፡፡በመቀጠልም ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ በዋናነት እንደሚታወቀው እቅድ ሶስት ሂደቶች (የዝግጅት፣ የትግበራና የማጠቃለያ ምዕራፎች) እንዳሉት እና ከነዚህም በመጀመሪያው የዝግጅት ምዕራፍ ብዙ ስራዎች እንደተሰሩና ማኔጅመንቱም ሰፊ ጊዜ ወስዶ ያለፈውን ገምግሞ ዝግጅቱን ወደ ሰራተኛው ማውረዱን፣ ከዕቅድ ዝግጅት ባለፈ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተገናኝቶ ሥልጠና መሰጠቱን መመሪያዎችንና የሥጋት ተጋላጮች ምንድናቸው? የሚሉት ታይተው መገምገማቸውንና የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ወ/ሮ አበባ ዓለማየሁ የለውጥ ትግበራ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኤጀንሲውን የ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ አመት የዕቅድ አፈፃፀምን በሚመለከት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፣ኤጀንሲው የ5 አመት ስትራቴጂያዊ እቅድ (ከ2008-2012) አዘጋጅቶ ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲተገብር ቆይቶ በ2011 በጀትዓመት ዕቅዱን እንደገና በመፈተሽ አሠራሩን ዘመናዊና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ የትኩረት መስኮችና ግቦችን በማሻሻል የግዥና የንብረት አስተዳደር ሥራዎችን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመምራት የሚያስችል የስራ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን አሰረድተዋል፡፡

Read more...

FPPPA has launched of the Electronic Government Procurement System (E-GP)Implementation Strategy with the Ministry of Innovation and Technology

The Federal Public Procurement and property Administration has  launched of the Electronic Government Procurement System (e-GP) Implementation Strategy and Roadmap  signing of the memorandum of understanding between the Ministry of Innovation and Technology and Federal Public Procurement and Property Administration held at Ministry of Finance and Economic Cooperation Building on 15th November, 2018 here in Addis Ababa..

Honorable W/r Marta Luwigi Genera Director of the Federal Public Procurement and Property Administration Agency addressed in her key note speech; she briefly updated on some of the activities were have been undertaking: The Federal Public Procurement and Property Administration Agency’s major reform areas fall into four main areas which are updating the legal framework, capacity development, monitoring and audit in ensuring compliance with proclamation, and introducing E-procurement system.

Read more...

ከተመረጡ የመንግስት መ/ቤቶች ጋር በግዥና ንብረት ኦዲት ግኝቶች ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ከተመረጡ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች ጋር በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አዳራሽ ከመስከረም 9–10/2011 ዓ.ም. የጋራ የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የመድረኩ ዓላማ በመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ዙሪያ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ዉይይት በማድረግ የሚፈቱበትን አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲያስችል የተዘጋጀ የምክክር መድረክ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ዋና ዳይሬክተሯ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቀጣይ የሆነ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፉን ከማሻሻል ጀምሮ የአዋጁ ማሰፈጸሚያ መመሪያዎችንና ማኑዋሎችን የማዘጋጀት፣ በወረዳ መዋቅር ካላቸው የስራ ባህሪ አጣጥመው ሊጠቀሙት የሚችሉትን የግዥ መመሪያዎችን የማዘጋጀት፣ የሙያ ስልጠናዎችን የመስጠት፣ የግዥና ንብረት አሰተዳደር ስራዎችን በዋና ዋና መለኪያዎች የመመዘን፣ የኤሌክትሮኒከ ግዥ ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ በተለይም ግልጸኝነትንና የመረጃ ተደራሽነትን በማስፋት ተወዳዳሪነትን ለማጠናከር በኤጀንሲው የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ትኩረት በመስጠት በተለይም በዘንድሮው በጀት ዓመት በሙከራ ትግበራ በመጀመር በቀጣይም በሁሉም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ለማስፋት ታስቦ የተጀመረውን ኢ-ፕሮክዩርመት ሁላችንም ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተን ልናሳካ ይገባል ብለዋል፡፡በመቀጠልም ዋና ዳይሬክተሯ አሁን ያለንበት ወቅት ከምን ጊዜውም በላይ በአገራችን የተጀመረውን የልማትና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ቀጣይነት ለማረጋገጥ የምንተጋበት፣ በተሰማራንበት የስራ መስክ የሕዝብ አገልጋይነታችንና ወገንነታችንን የምናጠናክርበት በተለይም ከተልዕኮአችን አንጻር በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር አፈጻጸም ዙሪያ የሚስተዋሉ የመልካም አሰተዳደር እጦት መገለጫ የሚሆኑና ለኪራይ ሰብሳቢነትና ብልሹ አሰራር በር የሚከፍቱ አሰራሮችን በመዝጋት በምትኩ ተገልጋይን ማዕከል ያደረገ አሠራርን እና መልካ አስተዳደርን በማስፈን፣ በሀገር አቀፍ የተጀመረውን የለውጥ አመራር እና የመደመር ጉዞ ከዳር ለማድረስ በጋራ በመመካከርና በመወያየት የሚያጋጠሙንን ችግሮች ለመፍታ አንዱ ከሌላው ተሞከሮ በመውሰድ የመንግስትን ውስን ሀብት በአገባቡ በመጠቀም ልማታችንን ለማፋጠን መረባረብ እንደሚጠበቅብን ገልጸዋል፡፡አቶ ነጋሽ ቦንኬ በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የግዥ አፈጻጸምና ንብረት ማስወገድ አቤቱታ ማጣራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ስልጠና የሰጡ ሲሆን ሰለ አቤቱታ ማጣራት፣ አቀራረቡና ሰለስነ-ሥርዓቱ፣ በግዥ ፈጻሚው መ/ቤት ሰለሚካሄድ የአቤቱታ ማጣራት ሂደት፣ ስለ ግዥ አፈጻጸምና ንብረት አወጋገድ አቤቱታ አጣሪና ውሳኔ ሰጪ ቦርድ፣ አቤቱታ ሰለሚቀርብባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፣አቤቱታ ማቅረብ ስለማይቻልባችወ ጉዳዮች፣ የጥፋተኝነት ሪፖርት ስለማይቀርብባቸው ሁኔታዎች የጥፋተኝነት ሪፖርት ሰለሚቀርብባቸው ጉዳዮች ላይ እና ሰለአቤቱታና የጥፋተኝነት ሪፖርት ማጣራት ሂደት አጠቃላይ ገጽታ እና በአፈጻጸም ሰለታዩ የአሰራር ችግሮች በዝርዝር አሰረድተዋል፡፡

Read more...

በግዥና ንብረት ኦዲት ግኝት ዙሪያ ከመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የጋራ ምክክር መድረክ ተካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ከመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር  በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አዳራሽ ከመስከረም 7–8/2011 ዓ.ም. የጋራ የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የምክክር መድረኩ ዓላማ በመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ዙሪያ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ምክክር በማድረግ የሚፈቱበትን አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲያስችል የተዘጋጀ የምክክር መድረክ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሯ በሀገራችን እየተመዘገበ ከሚገኘው ሁለንተናዊ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ጋር በተያያዘ መንግስት ከፍተኛ መጠን ያለው በጀት በየዓመቱ ለመንግስት ግዥ እንደሚመድብና ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው የመንግስት ገንዘብ የተዘረጋውን የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር የህግ ማዕቀፍን ተከትሎ ሥራ ላይ እንዲውልና ውጤታማ እንዲሆን ኤጀንሲው በአዋጅ የተሰጡትን ስልጣንና ሃላፊነት መሠረት በማድረግ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
በመቀጠልም በመንግስት ግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አስተዳደር ዙሪያ ለስራ ኃላፊዎች እና ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በመስጠት፣ የኮምፕሊያንስ ኦዲት በማድረግ በግኝቶቹ መሰረት የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ ክትትል በማድረግ ፍትሃዊ፣ ግልጽና ቁጠባን ማዕከል ያደረገ የግዥ እና ንብረት አሰተዳደር ሥርዓት እንዲኖር በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ያሉና በዚያው ልክ ቀላል የማይባሉ ለውጦችም እየተመዘገቡ ያለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ ዘለቀ ታፈሰ በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የግዥና ንብረት ኦዲትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን በ2010 ዓ.ም በፌዴራል የግዢ እና ንብረት ኦዲትና ክትትል ዳይሬክቶሬት በተደረገ የግዢ ኦዲት ወቅት ስለተገኙ ዋና ዋና ግኝቶች፣በ2010ዓ.ም በዋና ኦዲተር ኦዲት ወቅት በግዢ፣ በንብረትና በተሸከርካሪ ስምሪት ላይ ስለተገኙ ዋና ዋና ግኝቶች፣ በ2010ዓ.ም በመንግስት ግዥና ንብረት ኦዲትና ክትትል የግዢ ኦዲት ተደርገው የኦዲት ግኝት ስለታየባቸው መ/ቤቶችና የግኝቶቻቸው ደጋፊ ሰነዶች፣ በ2011ዓ.ም ኦዲት ወቅት ግኝቶችን በመቀነስ የተሻለ የግዢ፣የንብረትና የተሽከርካሪ ስምሪት አፈፃፀም እንዲኖር የጋራ ግንዛቤ እንዲኖር ስለማድረግ፣ በግዢ፣ በንብረትና በተሽከርካሪ ስምሪት ስርአቱ ውስጥ ያሉ በኦዲቱ የተለዩትን ግኝቶችና በምክክሩ የሚገኙ ምክረ ሐሳቦችን በማካተት የአቅም ግንባታውን ስራ የበለጠ ተደራሽ ስለማድረግ እና የኦዲት ግኝቶችን በሪፖርት ላይ በተገለፀው ጊዜ እርምት እርምጃ ወስዶ በወቅቱ ያለማሳወቅ ምክንያትን ለመለየትና ለወደፊቱ የመፍትሄ አቅጣጫ ስለማስቀመጥ አስረድተዋል፡፡

Read more...

More Articles...