The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

በአካባቢ የአየር ንብረት ለውጥና እንክብካቤ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአካባቢ የአየር ንብረት ለውጥና እንክብካቤ ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግማሽ ቀን የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ለመላው የኤጀንሲው ሰራተኞች ግንቦት 5 ቀን 2006 ዓ.ም በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሰጠ፡፡

የዕለቱ የክብር እንግዳ የፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጆንሴ ገደፋ በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የአካባቢ ጉዳይ የአጠቃላይ የህዝቡ ጉዳይ እንደሆነ በመግለፅ በአካባቢያችን ያለውን የተፈጥሮ ስጦታ በአግባቡ በመያዝ ኤጀንሲው የተቋቋመበትን አላማ ለማስፈፀም ስራዎችን ሚዛናዊ አድርጎ መያዝ እነደሚገባ በማሳወቅ ውጤታማ የሆነ ውይይት ከተሳታፊዎች እንደሚጠበቅ በማሳሰብ ስልጠናውን ከፍተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ባለሙያ የሆኑት ወ/ት ረሂማ መሀመድ እና አቶ አብርሀም ቸርነት ሥልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣አቶ አህመድ አሊ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የቴክኒክ ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሥልጠናው ዋና ዓላማ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስልትን የልማት ሞተር አድርጋ እንደምትተገብረው በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ በግልጽ ማሰቀመጧን በመግለፅ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትኩረት አግኝቶ ሊሰራ የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው ከስልጠናው ውይይት የሚገኙ ግብዓቶች ሊያዙ እንደሚችሉ አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ባለሙያ የሆኑት ወ/ት ረሂማ መሀመድ የአየር ንብረት ሙቀት ሳቢ ጋዞች፣ የአየር ንብረት አሉታዊ ተፅዕኖዎቹ ፣ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ ራዕይ ፣ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስልት፣የስልቱ አዘገጃጀት፣ ተቋማዊ ሁኔታ፣ የማጣጣሚያ ስልት እና በማጠቃለያው ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በሚኒስቴሩ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብርሀም ቸርነት በበኩላቸው በሀገራችን የአካባቢ አስተዳደር መቼ ተጀመረ? የአየር ንብረት ለውጥ ክስተቶች እና እንክብካቤው፣የኢትዮጵያ የአካባቢ ፖሊሲ፣ ሕግ…. ይዘት ምን ይመስላል? በአካባቢና ደን ሚኒኒስቴር ምን እየተሰራ ነው?እና የአካባቢና ደን ሚኒስቴር ስልጣንና ተጋባራት ላይ  ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም የሚገዙ እቃዎች ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ማስቻል፣የአገልግሎት ዘመናቸው ያላለቀ እና ለማለቅ ያልተቃረቡ፣ ወደ ሃገር የሚገቡት ቁሳቁሶች ከአካባቢ ጋር የሚጣጣሙ እንዲሆኑ በማገዝ በወቅቱ እንዲገዙ እና አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል የሚሉት ከኤጀንሲው የሚጠበቁ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

ለግማሽ ቀን በቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአካባቢ የአየር ንብረት ለውጥና እንክብካቤ ዙሪያ ላይ ያተኮረ  የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ላይ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ዳሬክተሮች፣ከፍተኛባለሙያዎች፣ባለሙያዎችና ሌሎች የኤጀንሲው ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

 

 

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአካባቢ የአየር ንብረት ለውጥና እንክብካቤ ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግማሽ ቀን የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ለመላው የኤጀንሲው ሰራተኞች ግንቦት 5 ቀን 2006 ዓ.ም በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሰጠ፡፡

የዕለቱ የክብር እንግዳ የፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጆንሴ ገደፋ በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የአካባቢ ጉዳይ የአጠቃላይ የህዝቡ ጉዳይ እንደሆነ በመግለፅ በአካባቢያችን ያለውን የተፈጥሮ ስጦታ በአግባቡ በመያዝ ኤጀንሲው የተቋቋመበትን አላማ ለማስፈፀም ስራዎችን ሚዛናዊ አድርጎ መያዝ እነደሚገባ በማሳወቅ ውጤታማ የሆነ ውይይት ከተሳታፊዎች እንደሚጠበቅ በማሳሰብ ስልጠናውን ከፍተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ባለሙያ የሆኑት ወ/ት ረሂማ መሀመድ እና አቶ አብርሀም ቸርነት ሥልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣አቶ አህመድ አሊ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የቴክኒክ ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሥልጠናው ዋና ዓላማ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስልትን የልማት ሞተር አድርጋ እንደምትተገብረው በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ በግልጽ ማሰቀመጧን በመግለፅ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትኩረት አግኝቶ ሊሰራ የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው ከስልጠናው ውይይት የሚገኙ ግብዓቶች ሊያዙ እንደሚችሉ አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ባለሙያ የሆኑት ወ/ት ረሂማ መሀመድ የአየር ንብረት ሙቀት ሳቢ ጋዞች፣ የአየር ንብረት አሉታዊ ተፅዕኖዎቹ ፣ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ ራዕይ ፣ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስልት፣የስልቱ አዘገጃጀት፣ ተቋማዊ ሁኔታ፣ የማጣጣሚያ ስልት እና በማጠቃለያው ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በሚኒስቴሩ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብርሀም ቸርነት በበኩላቸው በሀገራችን የአካባቢ አስተዳደር መቼ ተጀመረ? የአየር ንብረት ለውጥ ክስተቶች እና እንክብካቤው፣የኢትዮጵያ የአካባቢ ፖሊሲ፣ ሕግ…. ይዘት ምን ይመስላል? በአካባቢና ደን ሚኒኒስቴር ምን እየተሰራ ነው?እና የአካባቢና ደን ሚኒስቴር ስልጣንና ተጋባራት ላይ  ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም የሚገዙ እቃዎች ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ማስቻል፣የአገልግሎት ዘመናቸው ያላለቀ እና ለማለቅ ያልተቃረቡ፣ ወደ ሃገር የሚገቡት ቁሳቁሶች ከአካባቢ ጋር የሚጣጣሙ እንዲሆኑ በማገዝ በወቅቱ እንዲገዙ እና አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል የሚሉት ከኤጀንሲው የሚጠበቁ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

ለግማሽ ቀን በቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአካባቢ የአየር ንብረት ለውጥና እንክብካቤ ዙሪያ ላይ ያተኮረ  የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ላይ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ዳሬክተሮች፣ከፍተኛባለሙያዎች፣ባለሙያዎችና ሌሎች የኤጀንሲው ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

 

 

በአዋጅና መመሪያዎች ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ አሁን በስራ ላይ ባለው እና በተሻሻለው ረቂቅ የግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅና መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር መጋቢት 18-19 ቀን 2006ዓ›ም በኢትዮጵያ ካርታ ስራ ኤጀንሲ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አደረገ፡፡

የዕለቱ የክብር እንግዳ የፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ አበበ በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት ረቂቅ ሰነዱ በኤጀንሲው ሁለት የማሻሻያ ቡድኖች እንደተዘጋጀ ገልፀው ያለቀና የደቀቀ ሰነድ ነው ተብሎ እንዳይታሰብ በማሳሰብ ሰነዶቹ በድጋሚ በተሻለ ሁኔታ የሚታዩበት መንገድ እንዳለ በማሳወቅ የውይይቱ ዋና ዓላማ ለአዋጁና ለግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያዎች ግብዓት ለማሰባሰብ መሆኑን በመግለፅ ተሳታፊዎች ውጤታማ የሆነ ውይይት አዳዲስ ሀሳቦች፣ጥያቄዎችና አስተያቶች አንስተው ያነሱዋቸውን ሃሳቦች በድጋሚ በፅሁፍ ለመንግሰት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ እንዲልኩ አሳስበዋል፡፡

በፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የግዥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ነብዩ ኮከብ አሁን በስራ ላይ ባለው እና በተሻሻለው ረቂቅ የግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ መካከል ያሉ ልዩነቶችንና የተጨመሩ አዳዲስ ሀሳቦችን በማንሳት ትርጓሜን፣የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር መርሆዎችን፣የምንግስት መ/ቤት የበላይ ኃላፊ ሃላፊነትን፣የግዥና ንብረት አስተዳደር ተግባርና ሀላፊነትን በአጠቃላይ እስከ አዋጁ ምዕራፍ 15 ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ላይ በነባሩና በተጨመሩ አዳዲስ ሀሳቦች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በኤጀንሲው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር የግዥ አፈፃፀምና የንብረት አወጋገድ አቤቱታ ማጣራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወልደአብ ደምሴ በበኩላቸው አሁን በስራ ላይ ባለውና በተሻሻለው ረቂቅ የግዥ መመሪያ መካከል ያሉ ዋና ዋና ልዩነቶች ማለትም የግዥ አፅዳቂ ኮሚቴ ተግባርና ኃላፊነት፣የተርንኪ ግዥና ትርጓሜው፣ በመንግስት ግዥ አፈፃፀም ላይ የሚቀርብ አቤቱታና ስለ ውሳኔ ሰጪ ቦርድ፣ የቦርድ አባላት ስያሜና ዘመን፣ የግዥ ዘዴዎችና አፈፃፀማቸው በአጠቃላይ ከመመሪያው መግቢያ እስከ ክፍል 12 ድረስ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ትዕግስት ደበበ በበኩላቸው የፌደራል መንግስት የንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 9 /2003 ላይ የተደረጉ ዋና ዋና ማሻሻያዎች በትርጋሜ፣መርሆዎች፣የንብረት አስተዳደር ተግባርና ኃላፊነት፣የመንግስት ንብረቶች አስወጋጅ ኮሚቴ አወቃቀርና ተግባርና ኃላፊነት፣የንብረት አስተዳደር እቅድ ስለማዘጋጀትና ዕቅዱ ስለሚፀድቅበትና ስለሚሻሻልበት ሁኔታ በአጠቃላይ ከአንቀፅ 1 እስከ 60 ባሉት አንቀፆች ላይ በነባሩና በተሻሻለው አዳዲስ ሀሳቦች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል::

 

በኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ አበበ አወያይነት በቀረበው፣አሁን በስራ ላይ ባለውና በተሻሻለው የግዥና የንብረት አስተዳደር አዋጅና መመሪያዎች ላይ ከተሳታፊዎች በርካታ አስተያቶች፣ጥቄዎችና ገንቢ ሃሳቦች ተነስተው ለግንዛቤ ማብራሪያ ለሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎች በአቅራቢዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በመጨረሻም በመዝጊያው ሥነ ሥርዓት ላይ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ፀጋዬ አበበ  የሀገሪቱን የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓትን ለማሻሻል ተሳታፊዎች ላደረጉት አሰተዋፅኦ በማመስገን ለተሰጡት ግብዓቶች  ማሻሻያ ቡድኑ ላይ ተጨማሪ ሰዎችን በማካተት እንደገና እንደሚታይ በማሳወቅ ሚያዚያ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ተሳታፊዎች ለኤጀንሲው የማሻሻያውን የፅሁፍ አስተያየት ጥያቄና ሀሳቦች የሚልኩበት ቀን መሆኑን አሳስበዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲና ባለድርሻ አካላት ባደረጉት አሁን በስራ ላይ ባለው እና በተሻሻለው ረቂቅ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ውይይት ላይ  ከ130 በላይ ተሳታፊዎች ውይየቱን ተካፍለዋል፡፡


ከፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤ.ሕዝብ ግንኙነት ኮሚዩኒኬሽን  ዳሬክቶሬ