The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

Korean Investors Visit Agency

 

 

Korean Investors group who are interested in the investment of PV (Photo Voltaic) module manufacturing Plant visited The Federal Public Procurement and Property Administration Agency on Wednesday October 1/2014 here in Addis Ababa.

Ato Tsegaye Abebe General Director of Public Procurement and Property Administration Agency in his wel-coming speech said Ethiopia is suitable for foreign investment and addressed vision, mission and values of the Agency.

He also reminded the two Countries relations back during the Koreans’ War in which Ethiopians’ participated in the side of South Korea.

The Private investors described the purpose of their visit is to establish PV Module manufacturing facility in Ethiopia.This contributes to accelerate industrialization of Ethiopia PV industry through Korea-Ethiopia’s development cooperation, establishing foundation of technical on fabrication of solar module and shown interest to contact KOICA (Korean International Cooperation Agency) to support the Agency on e-procurement Feasibility Study.

 

Change Management and Planning Directorate Director Ato Admasu Mamo gave details about the Importance of Public Procurement System is, to improve the capacity of Local producers, suppliers, contactors and consultants, to attract Foreign direct investment and to enhance Good governance, to build trust between Government and Donors to increase the flow of Official Development Assistance (ODA) through Bilateral and Multilateral Relations.

Ato Admasu also said about General features of Public Procurement and its Legal Framework, Procurement Audit Process, Complaint Handling method, Major Challenges and the way forward.

During the discussion questions and comments have been raised and answers were given.

 

ለመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ሠራተኞችና ተገልጋዮች በሙሉ

እንኳን ለ2007 አዲስ አመትና የመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ፣

አዲሱ ዓመት የሰላም እና የዕድገት እንዲሆን ምኞቱን ይገልፃል፡፡

መልካም አዲስ አመት

ለመላው የኤጀንሲው ሠራተኞችና ተገልጋዮች

እንኳን ለ2007 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ!

በግዥ አፈፃፀም ሂደት በሚታዩ ችግሮችና የሙስና ስጋቶች ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶችና በአቅራቢዎች የሚታዩ የአፈፃፀም ችግሮችና የሙስና ስጋቶችን አስታወቀ

 

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክትር አቶ ፀጋዬ አበበ በግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶችና በንግዱ ማህበረሰብ /አቅራቢዎች/ በተደጋጋሚ በሚታዩ ዋና ዋና የአፈፃፀም ችግሮችና የሙስና ስጋቶች ዙሪያ ነሀሴ 6 ቀን 2006 ዓ.ም በኢትየጵያ ካርታ ስራ ኤጀንሲ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል ፡፡

አቶ ፀጋዬ የመንግስት ግዥና ንብረት የሚመራባቸው የህግ ማዕቀፎችና የአፈፃፀም ሰነዶች፣የመንግስት ግዥ መሰረታዊ መርሆዎች፣ዓላማዎችና ዋና ዋና ተግባራት፣የግዥ ፈፃሚ መ/ቤት ኃላፊነት፣የተፈቀዱ የግዥ ዘዴዎች፣በመንግስት የግዥ የአፈፃፀም ሂደት የሚታዩ ችግሮችና የሙስና ስጋቶች፣የግዥ ችግሮቹን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ የመፍትሄ እርምጃዎችና በኤጀንሲው በ2007 በጀት ዓመት በዕቅድ የተያዙ ዋና ዋና ስራዎች ላይም  ገለፃ ሰጥተዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ሌሎች ተጫራቾችን በሚገድብ ወይም አንድን ተጫራች በሚጠቅም መልኩ የቴክኒክ ፍላጎት ዝርዝር ሰፔሲፊኬሽን ማዘጋጀት፣በአንድ ጥቅል ጨረታ መግዛት የሚቻለውን በትንንሽ በርካታ ጨረታዎች በመከፋፈል ግዥ መፈፀምና በጥቃቅን ምክንያት ብቁ አቅራቢዎችን ከጨረታ ውጭ ማድረግ  በግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶች ከሚጠቀሱ ከብዙዎቹ በጥቂቱ  የአፈፃፀም ችግሮችና የሙስና ስጋቶች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም በአቅራቢዎች ወይም በንግዱ ማህበረሰብ ተጫራቾች እርስ በርስ በመመሳጠር የተጋነነ የግዥ ዋጋ ማቅረብ፣የተጭበረበረ የብቃትና ልምድ፣የህጋዊነት የጨረታ ወይም የውል ማስከበሪያ ሰነድ ማቅረብ፣ውል ከፈፀሙ በኋላ ተጨማሪ ዋጋ ካልተከፈለኝ በቀድሞ ዋጋ ማቅረብ አልችልም በማለት የዕቃ ወይም የአገልግሎት አቅርቦትን ማቋረጥ የሚጠቀሱ ችግሮችና የሙስና ስጋቶች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

አቶ ፀጋዬ ከንግዱ ማህበረሰብ ወኪሎች እንዲሁም በክልልና የከተማ መስተዳድር የመንግስት ግዥና ንብረት የስራ ኃላፊዎች ጋር በሚያጋጥሙ ችግሮች የምክክር መድረክ ማድረግ፣ከመንግስት ግዥ አፈፃፀምና ንብረት አስተዳደር ስራ ጋር ግንኙነት ላላቸው የመ/ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተከታታይ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና መስጠትና… ወዘተ ችግሮችን ለመፍታት

እየተወሰዱ ያሉ የመፍትሄ እርምጃዎች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በክቡር ደ/ር አብርሃም ተከስተ በገ/ኢ/ል/ሚር በልማት ዕቅድና የኢኮኖሚ አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ አወያይነት ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡

በመጨረሻም ክቡር አለማየሁ ጉጆ በገ/ኢ/ል/ሚር የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደርና ቁጥጥር ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ከተሳታፊዎች የተነሱ ጥያቄዎችንና አሰተያየቶች ተገቢ መሆናቸውን ገልፀው ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተው ግዥ በመንግስት ከፍተኛ ጥንቃቄና ትኩረት የሚሰጠው ዘርፍ መሆኑን በመግለፅና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ መሆኑን ጠቅሰው ትኩረት ሰጥቶ መስራት ጠቃሚ መሆኑን በማሳወቅ በግዥና ንብረት አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን በመንግስት፣በግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶችና በአቅራቢዎች እጅ ለእጅ መያያዝ መፈታት ያለበት ዘርፍ መሆኑን አሳስበዋል፡፡

ለግማሽ ቀን በቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የገ/ኢ/ል/ሚር፣የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ፣ የግዥ ፈፃሚ መ/ቤቶችና የአቅራቢዎች የምክክር መድረክ ላይ ከ135 በላይ   ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

 

 

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

 

የ2006 የዕቅድ አፈጻጸምና የ2007 ዕቅድ መርሀ ግብር ላይ ውይይት ተደረገ

የኤጀንሲው ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም በአማካኝ 92% ሲሆን

የፋይናስ አጠቃቀም 91.3%፣ መሆኑ ተገለፀ

 

የፌዴራል መንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የ2006 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን፣ የ2007 በጀት ዓመት ዕቅድንና ስትራቴጂያዊ የአፈጻጸም ማዕቀፍን በሚመለከት ነሐሴ 2 ቀን 2006 ዓ.ም ለመላው የኤጀንሲው ሠራተኞች ጋር በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር አዳራሽ ውይይት አደረገ፡፡

የዕለቱ የክብር እንግዳ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ አበበ በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የውይይቱ ዓላማ ባለፈው የ2006 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሥራ ምን ይመስላል? በ2007 በጀት ዓመትስ ምን ሊሰራ ታስቧል? በሚለው ላይ ለመወያየት ሲሆን፣ አያይዘውም ሀገራችንን አሁን ካለችበት የኢኮኖሚ ደረጃ ወደ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለማሳለፍ ሁሉም ዜጋ እንቅስቃሴ ሲያደርግ በመሆኑ ሃገራዊ ዕቅድን ለማሳካት ይህንን መርህ መከተል እንዳለብን አሳስበዋል፡፡

አቶ አድማሱ ማሞ የለውጥ ትግበራ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በኤጀንሲው የተከናወኑ የ2006 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ሪፖርት በሚመለከት በለውጥ ሠራዊት ግንባታ የ1 ለ5 አደረጃጀትን፣ከሕዝብ ክንፍ ጋር ስለተደረጉ የቋሚ ምክክር መድረኮች፣ ለተለያዩ ፈጻሚ አካላት ስለተሰጡ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች፣ ለደንበኞችና ተገልጋዮች ስለተሰጡ ሙያዊ ድጋፎች፣ ከፌዴራል የመንግሥት መ/ቤቶች በግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አስተዳደር ዙሪያ ስለተደረጉ የኦዲትና የክትትል ሥራዎች፣ ተጫራቾች በግዥ ፈጻሚ የመንግሥት መ/ቤቶች ላይ ያቀረባቸው አቤቱታዎችና ግዥ ፈጻሚ የመንግስት መ/ቤቶች በአቅራቢዎች ላይ

ባቀረቡአቸው የጥፋተኝነት ሪፖርቶች ላይ ስለተሰጡ ወሳኔዎች፣ስለተቀረጹ የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም፣ በአፈጻጸም ሂደት ስለአጋጠሙ የአሰራር ክፍተቶችና የተወሰዱ ወቅታዊ የማስተካከያ እርምጃዎችን በሚመለከት በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

በመቀጠልም ኤጀንሲው በ2006 በጀት ዓመት ውስጥ ያከናወናቸውን የዕቅድ አፈጻጸም ከአራቱ እይታዎች አንፃር የተገልጋይ ዕይታ 95%፣ የፋይናንስ ዕይታ 91.3%፣ የውስጥ አሰራር ዕይታ 85%፣ የመማማርና ዕድገት ዕይታ 97%፣ የ4ቱም ዕይታዎች አማካይ 92%መሆኑንም  አስረድተዋል፡፡

አቶ መሥፍን መኮንን የለውጥ ትግበራ ዕቅድ፣ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት በበኩላቸው ስለ ስትራቴጂያዊ የአፈጻጸም ማዕቀፍ ተልዕኮ፣ራዕይና እሴቶች እንዲሁም  ስለ 2007 በጀት ዓመት ግቦች፣ ዒላማዎችና የክትትል ሥልትን በተመለከተ በዝርዝር ገለፃ አድርገዋል፡፡

በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ በተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በመጨረሻም የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተርና ም/ዋና ዳይሬክተር የተሰጠው ሪፖርት ጥሩ እንደነበረና በ2007 በጀት ዓመትም ብዙ መሥራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል፡፡

ለግማሽ ቀን በቆየው የኤጀንሲው የ2006 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2007 በጀ ዓመት ዕቅድ ውይይት ላይ ከ90 በላይ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

 

 

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት