The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

የ2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል መሪ ቃል

 

ከፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተሬት

በሀገራዊ ፖሊሲ ሰነዶች ላይ ስልጠና ተሰጠ

በሀገራዊ ፖሊሲ ሰነዶች ላይ ስልጠና ተሰጠ

የፌደራል መንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በኢትዮጵያ ህዝቦች ትግልና ሀገራዊ ህዳሴ፣በልማታዊ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ትግልና ፈተናዎቹ፣ በህገ መንግስታዊ መርሆዎችና ሴኩላሪዝም፣የልማታዊ ሲቪል ሰርቪስ የመገንባት ፋይዳና የሲቪል ሰርቪሱ ሚና፣እና የተሀድሶው መስመር በኢትዮጵያ በሚሉት ሰነዶች ላይ ከጥቅምት 11 ህዳር 4 ቀን 2007 ዓ.ም ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር እና ከተጠሪ መ/ቤቶቹ ጋር በመተባበር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
አሰልጣኞቹ የኢትዮጵያን ጥንታዊና ዘመናዊ ታሪክን በአጭሩ፣ የኒዮ ሊበራሊዝምን አማራጭ በኣፍሪካና በኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያን የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደትና በመመዝገብ ላይ ያሉ መሰረታዊ ለውጦች፣ ህገ-መንግስታዊ ሥርዓት በኢትዮጵያ፣ የተሃድሶ መስመሩና የአገራዊ ህዳሴ ጉዟችን ምዕራፍ፣ የልማታዊ ሲቪል ሰርቪስ ምንነትና አስፈላጊነት እና ሌሎች ርዕሶች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡The MoFED Training
ሰልጣኞችም በበኩላቸው ስልጠናው ሀገራዊ ፖሊሲውንና አቅጣጫውን ለማወቅና ለመገንዘብ ጥሩ አቅም እንደፈጠረላቸውና በየመ/ቤታቸው ወደ ተግባር ለመለወጥና የመንግስትን ሀገራዊ ፖሊሲ  አቅጣጫ በአግባቡ ተረድተው ወደ ስራ ለመሰማራት በእጅጉ እንደሚረዳቸውና እንደሚጠቅማቸው   ገልፀዋል፡፡

በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ  በተሳታፊዎች የቡድን ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እንዲሁም በአፈጻጸም ላይ ስለአጋጠሟቸው ችግሮች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ለ20 ቀናት በቆየው የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር እና የተጠሪ መ/ቤቶች የሀገራዊ ፖሊሲ ስልጠና ላይ ከ1000 በላይ የሚሆኑ ከፍተኛ እና፣መካከለኛ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡


የፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ብሔራዊ የባንዲራ ቀን ተከበረ

 

መንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ

ብሔራዊ የባንዲራ ቀን ተከበረ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርና ከመንግሥት የግዥና የንብረት ማስወገድ አግልግሎት ጋር በመተባበር በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በታችው ግቢ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በድምቀት አከበረ፡፡

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ አበበ ሶስቱንም መ/ቤቶች በመወከል በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ፡ — "እኛ ኢትዮጰያውያን፣ የድህነትና ኋላ ቀርነት ዘመን ከአገራንችን ተወግዶ፣ ኢትዮጵያችን በልማትና በዲሞክራሲ ጐዳና በፍጥነት ተራምዳ፣ ሩቅ በማይባል ጊዜ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ተርታ ትሰለፍ ዘንድ የጀመርነውን የኢትዮጵያ ህዳሴ ወደ ማይቀለበስበት ደረጃ እናደርሳለን! የቀሪውን የአንድ ዓመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዳችንን ከመንግሥታችን ጐን ተሰልፈን ለማሳካት በሀገራችን ሰንደቅ ዓላማ ፊት ቃል እንገባለን፡፡" የሚለውን ቃለ መሃላ በዓሉን ለማክበር ለተሰበሰቡት የሶስቱም መ/ቤት ሠራተኞች አስነብበዋል፡፡

በዚህ ዛሬ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም በተከበረው የብሔራዊ የባንዲራ ቀን በዓልን ከላይ የተጠቀሱት የሶስቱ መ/ቤት ሠራተኞች በድምቀት አክብረዋል፡፡

 

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

For all Federal budgetary Organizations,Do you know this?

What is budget?

  1. An estimate, often itemized, of expected income and expense for a given period in the future.
  2. A plan of operations based on such an estimate.
  3. An itemized allotment of funds, time, etc., for a given period.
  4. The total sum of money set aside or needed for a purpose: the construction budget.
  5. A limited stock or supply of something: his budget of goodwill.
  6. Obsolete. A small bag;From dictionary.com

With this in mind:-

1. Public bodies shall have to prepare an annual procurement plan showing their procurement for the concerned budget

Year and containing such details as are stated in the directive to be issued by the Minister.

2. The Procurement Plan to be prepared by the Public bodies shall have to be approved by the head of the public body

Concerned and communicated to the relevant departments of the public body and the Federal Public Procurement and Property Administration Agency until Hamle 30 of the Ethiopian Calendar.

Public relations and communication directorate ( PPA )

የ2007 ዓ.ም የሰንደቅ ዓላማ ቀን መሪ ቃል

 

በሕዝቦችዋ ተሳትፎና ትጋት

ድህነትን ድል  በመንሳት

ብሄራዊ  ክብርዋንና ሰንደቅ-ዓለማዋን

ከፍ ከፍ በማድረግ ላይ ያለች ሀገር!!

ኢትዮጵያ!