The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

በሴቶች አመራርና ራስን መቻል፣ በኤች አይቪ/ኤድስ እና ስነ-ተዋልዶ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጋር በጋራ በመሆን በሴቶች አመራርና ራስን መቻል፣ በኤች አይቪ/ኤድስ፣የቤተሰብ ምጣኔና ሥነ ተዋልዶ ዙሪያ ግንቦት 23 ቀን 2008 ዓ.ም. በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አዳራሽ ሥልጠና ሰጠ፡፡
አቶ ደረጀ ተክሌ በኢንተርናሽናል ሊደርሺፕ ኢንስቲተዩት ሌክቸረር በሴቶች አመራርና ራስን መቻል በሚል ርዕስ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ በራስ መተማመን ማለት ምን ማለት ነው? በራስ የሚተማመን ሰው ምን ዓይነት ሰው ነው? በራስ መተማመን ማለት ሃሳብና ፍላጎትን በነጻነት መግለጽ፣መብትና ግዴታን ማወቅ፣ የሌሎችን ስብዕናን ማክበር እንዲሁም በራስ መተማመን መገለጫው በለውጥ ማመን እንደሆነና በራስ መተማመን ደግሞ ከትምህር ቤትና ከህይወት ልምድ እንደሚገኝም ገለጻ አድርገዋል፡፡  
በመቀጠልም አሰልጣኙ ሴቶችና አመራር በሚል ስለ አመራር ምንነት፣የአመራር ክህሎትና መገለጫው፣ የአመራር ከህሎት ከየት እንደሚጀምር፣እንዴት ብቁ መሪ መሆን እንደሚቻል እንዲሁም ሴቶች የማህበረሰቡ ግማሽ አካል እንደሆኑ፣ሴቶች ለአመራር ብቁ ስለመሆናቸው፣ የአመራር ክህሎት በሴቶች ዘንድ አና ሴቶችን በአመራር ለማበረታት የአመለካከት ለውጥ ላይ ስለመስራት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ሲስተር ሂሩት አለማየሁ ከኤች አይቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት በበኩላቸው ስለ የቤተሰብ ምጣኔና ሥነ ተዋልዶ፣ ስለ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ወቅታዊ ሁኔታ፣ በኢትዮጵያ ሰለ ሥርጭቱ ሁኔታ፣ስለ አጋላጭና ተጋላጭ ባህሪያት፣የመጋለጥ ሁኔታ ከሴቶች አንጻር፣ በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ዙሪያ ስላለው መረጃ እና የህበረተሰቡ ሚና የሚለውን በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
አሰልጣኟ ስለ ሥነ-ተዋልዶና የቤተሰብ ምጣኔን በሚመለከት ስለ ሴትና ወንድ ሥነ-ተዋልዶ አካላት፣ የቱኩረት ነጥቦች ከሥነ-ተዋልዶ አንጻር ትምህርትም በተለያዩ የወጣት ማዕከላትና ጤና ጣቢያ እንደሚሰጥ ገለጻ አድርገዋል፡፡