The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

25ኛው የግንቦት 20 የብር ኢዮቤልዩ በዓል ተከበረ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴርና ከመንግሥት የግዥና የንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጋር በመተባበር በአገር አቀፍ ደረጃ ለ25ኛ ጊዜ የሚከበረውን የግንቦት 20 በዓልን ግንቦት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር አዳራሽ አከበረ፡፡
የዕለቱ የክብር ዕንግዳ ክቡር አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ሚኒስትር በበዓሉ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የበዓሉ ዓላማ የሩብ ክፍለ ዘመን ስኬቶቻችን አሁን ለደረስንበት ደረጃ እንዴት እንዳበቁን በማሳየት ያሉብንን ችግሮች የሚፈታ ድሎቻችንን የሚያጎለብትና የሚያስቀጥል የህዝብ መነሳሳት፣የተሻለ መግባባትና የባለቤትነት መንፈስ መፍጠር መሆኑን  አስታውቀው ለበዓሉ ታዳሚዎች ለመድረኩ የተዘጋጀውን ፅሁፍ በጥሞና እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡  
አቶ ተስፋዬ ብርሀኑ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር በዓሉን በማስመልከት ከማሽቆልቆል ጉዞ ወደ ዕድገት ምዕራፍ ሩብ ምዕተ ዓመት የትግልና የድል ጉዞ በሚል ርዕስ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡   
ም/ዋና ዳይሬክተሩ ህዝብ የተጠቀመበት የ25 ዓመታት የዕድገት ጉዞ፣ልማት ተስፋፍቶ ማሽቆልቆል የተገታበት ሩብ ምዕተ ዓመት፣ጉዞን የገታ የመሰረተ ልማት የተስፋፋበት ሩብ ምዕተ
ዓመት፣ጉዞን የገታ ዲሞክራሲ እውን የሆነባቸው ሀያ አምስት ዓመታት፣ጉዞን የመግታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከተ መልካም አስተዳደር የታየባቸው ሀያ አምስት ዓመታት እና ዓለም አቀፋዊ ግንኙነታችን የዳበረበት ሩብ ምዕተ ዓመት በሚሉት ርዕሶች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡
አቶ ተስፋዬ ለተመዘገቡ ድሎች ያበቁን ዋና ዋና ምክንያቶች የትክክለኛ አመራር፣ፈፃሚ ሀይልና የአፈፃፀም አቅጣጫ ውጤት መሆኑ፣ርዕዮተ አለማዊ ትጥቅ የጨበጠ ድርጅት የመራው እንቅስቃሴ መሆኑ፣ብቃቱ የተመሰከረለት ድርጅት የመራው ለውጥ መሆኑ፣ሁሉ በብስለትና በፅናት ባለፈ ድርጅት የተመራ የተሀድሶ ጉዞ መሆኑና ሌሎች ለተመዘገቡ ድሎች ያበቁን ዋና ዋና ምክንያቶች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም ከበዓሉ ታዳሚዎች በተነሱት የተለያዩ አስተያየቶች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቶ በበላይ አመራሮች ለበዓሉ የተዘጋጀው ኬክ ከተቆረሰ በኋላ ከብሄራዊ ሎተሪ የተላኩት በርካታ ሎተሪዎች ላይ ሽያጭ ተከናውኖ የዕለቱ ስብሰባ ከቀኑ 6፡30 ሰዓት ተጠናቋል፡፡ለግማሽ ቀን በቆየው የ2008 ዓ.ም 25ኛው ዓመት የግንቦት 20 በዓል ላይ የሶስቱም መ/ቤቶች አመራሮች፣ኃላፊዎችና ሠራተኞች በዓሉን በድምቀት አክብረዋል፡፡

የሕዝብ ግንኙነት ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት