The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የ2013 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከበላይ ኃላፊዎች፣ ከማኔጅመንት አባላት እና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር የ2013 የበጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትን በተመለከተ ጥር 4 ቀን 2013 ዓ.ም በገንዘብ ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡

በኤጀንሲው ዳይሬክተሮች በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የተከናወኑ ሥራዎችን፣ ያጋጠሙ ችግሮችን፣ የመፍትሄ ሃሳቦችን፣ ትኩረት ሊደረግባቸው ስለሚገቡ ጉዳዮችና ከመደበኛ ሥራ ውጭ ስለተከናወኑ ሥራዎች ከተገልጋይ፣ ከውስጥ አሰራር፣ ከፋይናንስ እና ከመማርና ዕድገት ዕይታዎች አንጻር ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በመቀጠልም የኤጀንሲው የበላይ ኃላፊዎች በቀረበው ሪፖርት ላይ ከተሳታፊዎች የተሰጡ አስተያየቶችን የተቀበሉ ሲሆን፣ ለተጠየቁ ጥያቄዎችም መልስ በመስጠትና ተጨማሪ ሀሳቦችን በማከል ወይይቱን አሳታፊ አንዲሆን አድርገውታል፡፡

በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከሠራተኞች  አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ጥያቄዎችም ተነስተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ለግማሽ ቀን በቆየው የ2013 የበጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትን በተመለከተ ውይይት ላይ የበላይ ኃላፊዎች፣ የማኔጅመንት አባላት እና ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

 

የኢፌድሪ የመ.ግ.ን.አ.ኤ.የህዝብ ግንኑነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት