The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የምክትል ዋና ዳይሬክተሩ መልዕክት

የመንግስት ግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አስተዳደር ተግባራት ከፌደራል መንግስት ዓመታዊ በጀት ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወሰድ ጥናቶች የሚያመለክቱ ሲሆን ይህ ከፍተኛ የመንግስት ሃብት ቁጠባንና ቅልጥፍናን በተላበሰ መልኩ ያለብክነት ስራ ላይ እንዲውል የመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደርን በመርህ ማከናወን የግድ ነው፡፡ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋነኛ መርህ ደግሞ በግዥ አፈጻጸም ረገድ የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ተመጣጣኝ ፋይዳ ወይም ጥቅም ማስገኘት እንደሆነ በአዋጁ አንቀጽ 5 ላይ ተገልጿል፡፡

በዚሁ መሰረት ኤጀንሲው ግልጽነት እና ተጠያቂነት የሰፈነበት፣ እንዲሁም ፍትሐዊ፣ ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ለማስቻል በአማካሪ በተከናወነ ጥናት መነሻነት የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥራዎች በዘርፉ በሰለጠኑ ሙያተኖች እንዲመራ የሚያስችል የኃላፊዎች እና ባለሙያዎችን አቅም ባገናዘበ ሁኔታ በBasic, Essential እና Advanced ደረጃዎች የፕሮፌሽናላይዜሽን ስልጠና በመስጠት የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም የመገንባት ሥራዎችን እያከናወነ ያለ ሲሆን፣ ከዚሁ ጎን ለጎን ግዥ ፈጻሚ መ/ቤቶች የግዥ አፈጻጸማቸውን የሚመዝኑበት ቁልፍ የግዥ አፈጻጸም መለኪያዎችን በማዘጋጀትና ክትትል የማድረግ ሥራ፣ የግዥና ንብረት አስተዳደር የህግ ማዕቀፍ የማሻሻል፣ በግዥ አፈጻጸምና ንብረት አወጋገድ ረገድ ከግሉ ዘርፍ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የማጣራት እና ውሳኔ አሰጣጥን ግልጽ እና ተዓማኒነት እንዲኖረው የማድረግ፣ የግዥና ንብረት ኦዲትና ቁጥጥር ሥራዎችን የማጠናከር፣ ዘመናዊ እና በኤሌክትሮኒክ የተደገፈ የመንግስት ግዥ ሥርዓት እንዲኖር የማድረግ፣ የከፍተኛ የሃብት ብክነት የሚታይበትን የመንግስት ተሽከርካሪ አጠቃቀምና ቁጥጥርን ሊያግዝ የሚችል fleet Management System የማበልጸግ እና ሌሎች በርካታ የሪፎርም እና ማሻሻያ ስራዎች እያከናወነ ይገኛል፡፡

ስለሆነም በዘርፉ ለሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት እነዚህን የሪፎርም እና ማሻሻያ ሥራዎችን በማጠናከርና፣ሥርዓቱን የበለጠ ዘመናዊና ቀልጣፋ በማድረግ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ከዓለም ዓቀፍ መመዘኛዎች አንጻር ተቀባይነት ያለውና ከበርካታ አገራት ጋር ተወዳዳሪ የሆነ የመንግስት ግዥና ንብረት አስዳደር ሥርዓት ለመዘርጋት ኤጀንሲው የበለጠ ጠንክሮ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን፣ ተገልጋዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተከናወነ ለሚገኘው የማሻሻያ ሥራ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ጥሪ ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

ክቡር አቶ ወልደአብ ደምሴ የኤጀንሲው ም/ዋና ዳይሬክተር