The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥልጠና ተሰጠ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሰበመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ዙሪያ ከተለያዩ የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች ለተውጣጡ የግዥ ዳይሬክተሮችና የግዥ አጽዳቂ ኮሚቴ አባላት ከታህሳስ 15-17 ቀን 2013 ዓ.ም. በአዳማ ከተማ ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥልጠና ሰጠ፡፡

ሥልጠናውን የሰጡት በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና የግዥና ንብረት ባለሙያዎች ሲሆኑ፣ ስለመንግስት ግዥ ምንነት? የመንግስት ግዥ ስለሚመራባቸው ህጎች፣ ስለመንግስት ግዥ መርሆዎች፣ ስለ መንግስት ግዥ አፈጻጸም ተግባርና ኃላፊነት፣ ስለግዥ ሥርዓትና ዑደት፣ ስለጨረታ ሰነድ ዝግጅት፣ ስለመንግስት ግዥ እና ስለመንግሥት ግዥ አጠቃላይ ገጽታ የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥልጠና በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

በዚህ የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥልጠና ላይ ግዥና ንብረትን በሚመለከት ለቀረቡት የመወያያ ጥያቄዎች ሠልጣኞች በቡድን በመወያየት  ምላሽ ሰጥተዋል፡፡በዚህ ሶስት ቀናት በቆየው ሥልጠና ላይ ሠልጣኞች የዕውቀት ሽግግርን አግኝተው በሥራቸው ላይ ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ ይታመናል፡፡

የኢፌድሪ የመ.ግ.ን.አ.ኤ.የህዝብ ግንኑነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት