The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የዋና ዳይሬክተሩ መልዕክት

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በሁሉም ግዥ ፈጻሚ የፌደራል ባለበጀት መ/ቤቶች በመንግሥት ግዥ አፈፃፀም እና ንብረት አወጋገድ ረገድ የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም በመገንባት፣ የግዥ አፈጻጸምና ንብረት አስተዳደር ውጤታማ በሆነ መንገድ የሚፈጸም ስለመሆኑ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ፣ በጥናት ላይ በመመርኮዝ ዘመናዊ እና ቀልጣፋ አሰራር ሥርዓት በመዘርጋት፣ በዘርፉ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና የአሰራር ማነቆዎችን ለመቅረፍ የሚያስችል ግልጽ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊና ተጠያቂነት የተረጋገጠበት የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደርን ለማስፈን እየሰራ ይገኛል፡፡

በመሆኑ በዘርፉ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና የአሰራር ማነቆዎችን ለማስወገድ በየበጀት ዓመቱ ለመንግስት ግዥ የሚመደበው ከፍተኛ መጠን ያለው መዋዕለ ንዋይ ተመጣጣኝ የሆነ ፋይዳ (Value for Money) እንዲያስገኝ ከማድረግም በዘለለ በከፍተኛ ወጪ የተገዛው ንብረት ከብክነት በጸዳ መንገድ ሥራ ላይ የሚውልበትን የአሰራር ሥርዓት በማጠናከር እንደ አገር በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ የታለሙ የቀጣይ 10 ዓመት መሪ ዕቅዶችን ግብ ለማሳካት እና ሁለተናዊና ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከፍተኛ ጥረት ማድረግን ኤጀንሲው የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ በትጋት  የሚሰራ መሆኑን እየገልጽኩ፤ ለዚህ እቅድ መሳካት ሥራዎችን በቅንጅትና በህብረት መስራት ወሳኝ በመሆኑ ኤጀንሲው የሚመለከታቸው የመንግስትና የግል ባለድርሻ አካላት በተለይ የሁሉም ግዥ ፈጻሚ የፌደራል መንግስት መ/ቤቶች አመራርና ፈጻሚዎች ዘርፉ አመርቂ ውጤት እንዲያስመዘግብና በላቀ ደረጃ ውጤታማ እንዲሆን የሚጠበቀባችሁና ሚና እንድትወጡ ጥሪዬን እያስተላለፍኩ ለዚህም መሳካት ኤጀንሲው ያለሰለሰ ጥረት እንደሚያደርግ ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡

ክቡር አቶ ሀጂ ኢብሳ ገንዶ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር