The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ

የፌዴራልመንግሥት የግዥና የንብረትአስተዳደርኤጀንሲለመላውየኤጀንሲውየበላይ ኃላፊዎች እና ሠራተኞችየ2011 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ አፈፃፀምን እና የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ነሐሴ 8 ቀን 2011ዓ.ም. በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስትየግዥናየንብረትአስተዳደርኤጀንሲዋናዳይሬክተርየውይይቱ ዋና ዓላማ የ2011 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ አፈፃፀምን እና የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ፣ የ12 ወራት ዕቅድ አፈጻጸማችን ምን እንደሚመስል እና በቀጣዩየበጀት ዕቅድ ዓመት ለምንሰራው ስራ አቅጣጫ መያዝ እንዳለብንለውይይቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡አቶ አሰድ አብደላ የዕቅድ ዝግጅትና ክትትልዳይሬክቶሬት ተ/ዳይሬክተር የ2011 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን በሚመለከትየ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ ለማዘጋጀት መነሻ ይሆን ዘንድ በ2010 አፈፃፀም የነበሩ ጥንካሬዎችንና እጥረቶችን በዝርዝር በመገምገም ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮችን ለይቶ በመውሰድ እንዲሁም በኤጀንሲው ልዩ ትኩረት የሚሹ የስጋት ተጋላጭነት አካባቢዎች መለየት የዕቅድ መነሻ ተደርጎ መወሰዱን፣ዕቅዱ ከተዘጋጀ በኋላ በማኔጅመንትእና በሠራተኞች በየደረጃው በማወያየት ዕቅዱን የማዳበር እና የባለቤትነት ስሜት እንዲፈጠር ጥረት መደረጉን፣ ከአራቱም ዕይታዎች /ከተገልጋይ፣ ከውሰጥ አሰራር፣ ከፋይናንስ እና ከመማርና ዕድገት/አንጻር እንዲሁም ሰለዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም፣ ስለግብ ተኮር ተግባራት ዕቅድ አፈፃፀም፣ ሰለተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፣ ሰለክትትልናየግምገማ አፈፃፀም፣ ሰለጋጠሙችግሮች፣ ሰለመፍትሄ እርምጃዎች እና ሰለቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ሰፋ ያለገለጻ አድርገዋል፡፡በመቀጠልም የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ሰለኤጀንሲው ዕቅድ ግቦችና ዋና ዋና ተግባራት የ2012 በጀት ዓመት የተከለሰ የኤጀንሲውን ዕቅድን ማዘጋጀት፣ የ2012 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት የሥራ መርሃ-ግብር እና ዓመታዊ፣እና ወርሃዊ የጥሬ ገንዘብዕቅድ ማዘጋጀት፣ የ2012 በጀት ዓመት የግዥ ዕቅድ ማዘጋጀት እና የ2011 በጀት ዓመት የግዥ አፈጻጸም ሪፖርት ማዘጋጀት፣በ2011 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሂደት ወቅት ከታዩ ክፍተቶች በመነሳት የአቅም ግንባታ ሥራ ለመስራት የሚያስችል ዳሰሳ ጥናት ማድረግ፤ በጥናቱ መሠረት ለ2012 በጀት ዓመት የአቅም ግንባታ ዝርዝር ዕቅድ ማዘጋጀት እና ለበጀት ዓመቱ ለሥራ ማስፈጸሚያነት የሚውሉ ግብዓቶችን ማሟላት እንደሆነ አሰረድተዋል፡፡በመጨረሻም ክብርትወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የ2011 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም በጥሩ ሁኔታ መቅረቡን ገልጸው፣ የኤጀንሲው ማኔጅመንትም ሪፖርቱን በዝርዝር አይቶ መቅረቡንና ምን ችግር አለ? እንዴትስ እንፍታው? የሚለው ታይቶ ለ2012 የበጀት ዓመት ዕቅድ መነሻተደርጎ መወሰዱን፣ በሪፎርም ሥራዎችም እና በአገልግሎት አሰጣጥም መገምገሙን እና በአጠቃላይ ሪፖርቱ በአብዛኛው በጥንካሬ መገምገሙን ገልጸዋል፡፡በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከሰራተኞች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ለግማሽ ቀንበቆየውየኤጀንሲውየ2011በጀትዓመት ዕቅድአፈጻጸም ግምገማ ሪፖርትእና የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይትላይ የኤጀንሲው የበላይ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡   

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት