The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የመንግስት የግዥና የንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ ሠራተኞች የመልካም አሰተሳሰብ መጀመርያ የሆነውን አካባቢን የማጽዳት ተግባር አካሄዱ

የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ሰራተኞች የመልካም አሰተሳሰብ መጀመርያ የሆነውን አካባቢን የማጽዳት ተግባር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሊያከናውነው የሚገባውን እና በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደውን አካባቢን የማጽዳት ዘመቻን በመደገፍ ግንቦት 9/2011 የኤጀንሲውን ቅጥር ግቢ በማጽዳት ተግባራዊ አድርገዋል፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት የግዥና የንብረት አሰተዳደር አጄንሲ ዋና ዳይሬክተር ግንባር ቀደም በመሆን፣ ሠራተኛውን በማበረታታ እና አብረው ቆሻሻን በማጽዳት ተግባር ላይ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡የተለያዩ የኤጀንሲው ዳይሬክቶሬቶች ዳይሬክተሮችና የኤጀንሲው ሠራተኞች ቆሻሻን በማጽዳትና መተላለፊያ መንገዶችን ዘግተው የተቀመጡ ነገሮችን በማንሳት አካባቢው ለእይታ እንዲመችና ጽዱ እንዲሆን አድርገዋል፡፡ በመጨረሻም የመንግስት የግዥና የንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ “አካባቢን ከቆሻሻ ውስጣችንን ከቂምና ከጥላቻ እናጽዳ” ከሚለው መርህ በመነሳት ይህ የጽዳት ዘመቻ ቆሻሻን ብቻ ሳይሆን አእምሮአችንን ለማጽዳት አመላካችና ጥሩ ምሳሌ መሆኑን እንዲሁም ውብና የበለጸገች ከተማን ተባብረን መፍጠር እንዳለብን መልዕክት አሰተላልፈዋል፡፡

በፌ.መ.ግ.ን.አ.የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት