የኤጀንሲው ሥልጣን
ኤጀንሲው ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ የሚከተለው ሥልጣን ይኖረዋል፡-
- ማናቸውም የመንግስት መሥሪያ ቤት ወይም አቅራቢ ሕግ ከሚያዘው ውጪ ስለመፈፀሙ፤ግዥ በትክክል ስላለማከናወኑ የግዥውን አሰራር በትክክል ስላለመፈፀሙ ወይም ስለመመሳጠሩ ጥቆማ የቀረበ እንደሆነ ከግዥው አፈፃፀም ጋር የተያያዙ መረጃዎች፤ሰነዶች፤መዝገቦች እና ሪፖርቶች እንዲቀርቡለት የማዘዝ፤
- ምስክሮችን የመጥራት፤ምስክሮችና ግዥውን የሚመለከታቸው ወገኖች ቃላቸውን በመሃላ እንዲሰጡ የማድረግ፤የሂሳብ መዝብ፤ፕላን፤ሰነድ እንዲቀርብለት የማድረግ፤
- ከገበያ ጋር የማይጣጣም ዋጋ በሚያቀርቡ እና ሌሎችም የዚህን አዋጅ እና በሚኒስትሩ የሚወጣውን መመሪያ ድንጋጌዎች፤አቅራቢዎች ወይም በመንግስት ንብረት ማስወገድ ሂደት ተሳታፊዎች ላ በቀረበ አቤቱታ መነሻነት ማስጠንቀቂያ የመስጠት፤ለተወሰነ ወይም የንብረት ማስወገድ ሂደት እንዳይሳተፍ የማገድ፤
- በመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር አፈፃፀም ላይ በራሱ ፕሮግራም ወይም በሚደርሰው ጥቆማ መነሻነት ኦዲት እንዲካሔድ ማድረግ፤
- በቂ ምክኒያት ያለ መሆኑን ሲረዳ በዚሁ አዋጅና በግዥ መመሪያው ከተፈቀዱ የግዥ ሥርዓቶች ውጪ ግዢ ለመፈፀም ከመንግስት መስሪያ ቤቶች በሚቀርቡ ጥያቄዎች መሰረት እንዲፈፀም መፍቀድ፡፡