The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የኤጀንሲው ተግባሮች

ኤጀንሲው ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ተግባሮች ያከናውናል፡-

በመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ፖሊሲዎች፤መርሆዎችና አፋፃፀሞች ላይ የፌደራል መንግስትን ማማከር፤ለክልሎች እና ለከተማ አስተዳደሮች የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት፤
በፌዴራል መንግስት ውስጥ ያለውን የመንግስት ግዥ አፈፃፀም እና የንብረት አስተዳደር ስርአት ተግባራዊነት መከታተል፤ለሚኒስትሩ ሪፖርት ማድረግ እና በ ሕግና በአፈፃፀም ስርአቱን ላይ ማሻሻያ ሀሳቦች ማቅረብ፤
አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የግዥ እና የንብረት አስተዳደር ስልጠና እንዲሁም የግዥና የንብረት አስተዳደር አፈፃፀምን ለመምራት የሚያስፈልገው ችሎታ በሙያው ለመሠማራት ተፈላጊ የሆነውን ፣ማስረጃ ዓይነት እና የሙያው ዕድገት ሊከተል የሚገባው ሂደር መወሰኑን ማረጋገጥ፤
መደበኛ የግዥ ሰነዶች፤አሠራሩን የሚመሩ ቅፆች እና ሌሎች ለግዥ እና ንብረት አስተዳደር አግባብነት ያላቸውን ሰነዶች ማዘጋጀት፤ሥራ ላይ እንዲውሉ እና ወቅታዊ እንዲሆኑ ማድረግ፤
ከተፈቀዱ መደበኛ የግዥ ዘዴዎች፤ሰነዶች፤አሰራሩን ከሚመሩ ቅፆች እና ሌሎች ለግዥ አፈፃፀም አግባብነት ካላቸው ሰነዶች ውጪ ግዥ ለመፈፀም ወይም ከተፈቀዱ የንብረት አወጋገድ ሥርዓቶችና ስልቶች ውጭ ንብረት ለማስወገድ በመንግስት መሥሪያ ቤቶች ጥያቄውን መርምሮ ውሳኔ መስጠት፤
በመንግስት ግዥ ለማሳተፍ ፍላጎት ያላቸው አቅራቢዎች የሚመዘግቡትን የተቀላጠፈ ሥርአት መዘርጋት በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ለመመዝገብ የሚቀርቡ ማመልከቻዎችን መቀበል መመርመር እና የምዝገባውን ዝርዝር ማሠራጨት፤
በዕጩ ተወዳዳሪዎችና በአቅራቢዎች ላይ የመንግስት መስራያ ቤቶች የሚያቀርቧቸውን አቤቱታዎች መርምሮ ውሣኔ መስጠት፤የውሳኔውን ቅጂ ለሚመለከታቸው ማሠራጨት፤
ከመንግስት መሥሪያ ቤቶች ጋር ባደረጉት የግዥ ውል መሠረት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው ስለብቃታቸው ሀሰተኛ መረጃ በማቅረባቸው ወይም በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፮(፫) እና ፴፪(፪) የተዘረዘሩት ድርጊቶች በመፈፀማቸው ምክኒያት ኤጀንሲው በመንግስት ግዥ አፈፃፀም እንዳይሳተፉ ያገዳቸውን አቅራቢዎች ዝርዝር መያዝና ማሠራጨት፤
ለግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አስተዳደር የሚያገለግል የመረጃ ማሰራጫ እና ክምችት ማቋቋም ማጎልበት መጠበቅ እና ወቅታዊነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ማድረግ
የተቋም እና የሰው ጋር ኃይል አቅም ለማጎልበት የሚያስችል የአቅም ግንባታ ፖሊሲና ዕቅድ እንዲኖር ማድረግ፤

የሙያና ከሙያ ጋር በተያየዙ አግባብነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ የተሠማሩ ሆነው በመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ለመሳተፍ ፍላጎት ካላቸው አካላት ጋር ተቋማዊ ግንኙነት መፍጠር እና ማዳበር፤ስለመንግስት ግዥ አፈፃፀም እነ ንብረት አስተዳደር ጥናት ማካሔድ የአቅም ግንባታ፤ትብብር እንዲኖር ማድረግ፤
ይህ አዋጅና በአዋጁ መሠረት የሚወጡ ደንቦች መመሪያዎች እንዲሁም በሚኒስትሩ የተሰጡት ሌሎች ተግባሮች በትክክል ስራ ላይ መዋላቸውን ማረጋጥ፤

ከመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚቀርብለትን መረጃ መሰረት በማድረግ የመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት እና መጠን እንዲሁም ንብረት አስተዳደር ጉዳዮች ልዩ መረጃዎችን መስጠት፤
በዚህ አዋጅ በመንግስት ግዥ አፈጻጸምና ንብረት አወጋገድ ላይ በዕጩ ተወዳዳሪዎች የሚቀርቡ አቤቱታዎችን እንዲያይ ለተቋቋመው ውሳኔ ሰጪ ቦርድ የጽህፈት ቤትና የቴክኒክ ድጋፍ አገልግሎት መስጠትና የቦርዱን ውሳኔዎች ተግባራዊነት መከታተል፤
አግባብነት ባላቸው የብሔር ክልላዊ መንግስታት አካላት በክልሉ የመንግስት ግዥ አገጻጸም ላ እንዳሳተፉ የታገደ እጩ ተወዳዳሪ ወይም አቅራቢ በፌደራል መንግስት መሥሪያ ቤቶች ግዥ እንዳይሳተፍ ማድረግ፤
በመንግስት መሥራ ቤቶች አገልግሎት ላይ ለሚውሉ ዋና ዋና ቋሚ ንብረቶች ደረጃ ማውጣት አፈጻጸሙን መከታተል፡፡